Tuesday, April 14, 2009

የፍቅር ነገር

እንዲህም አለ:

በእንተ ፍቅር የተራቡ
በእንተ ፍቅር የጠገቡ
ነው ይኼ መከተቡ:

ድሮ...
ለነገ ዕጣ ፋንታ ስኬት
ዘዴ ብልሀት ሲዶለት
ከጂስም* -ከሰራ አከላት
"ልብ' ተግሳጽና ቁጣ ደርሶት
ጭንቅላትን "በሽምደዳ' ለማገዝ
በየቤተ-መጽሐፍቱ ሲዋትት
ልብ እንደ ""ልብ"' ሳይጫወት ፊት ተነስቶ
የአካል-የሕይወት መዘውር እንዳልሆነ ነገር ተዘንግቶ
የመውደድ ቅዋው** ደክሞ ሳስቶ
""ነገ"" አዳምኖ በሳለው ገጽ ፈዞ
በማያውቀው "ነገ" ታዞ
ለማያውቀው"'ነገ"" ተክዞ
ከነማፍቀሩ ተቀብሮ""በነገ"" ተገንዞ
ትንሽ እንኳ ሳይዘከር ተትቶ
ነገ ዛሬ ሆኖ ከዘመን በኍላ ትንሳዔ አግኝቶ
የመውደድ ኃይሉም አገርሽቶ
ቢወድ አንዲት ድማም
የለዛ ባለጠጋ ሀብታም
በግርማዋ ከልብ ተስቦ
ቢፈልግ ሊያወራት ቀርቦ
ሰኔና ሰኞ; "'አንተን አላውቅ; ፍቅርም አልፈልግ"" ተባለ
እንዲህም አለ
መተያየት; መነጋገር ማንን ገደለ?!
የኔ ፍቅር;
የልቤን ጥጋጥግ መሀሉም ሳይቀረው እያተራመሰ
እንጥል የምታህል ትንሽ እንኳ ፍቅር ልቧ ካልደረስ
በኔ 'ሚንቀለቀል የፍቅር ነበልባል ምንም ካልደረሳት
"የሷ ባይሆን ብዬ" አሁን ጠረጠርኩት
እንግዲህ አምላክ ባርኮ ለሌላዋ ይስጣት!!
~~~~~ ~~~~~ ~~~~~


መፍቻ:
*ጂስም- ሰውነት
**ቅዋው- አቅሙ

(ጊዜያቸውን ላይብራሪ ለላይብራሪ ላቃጠሉ; ለተሸወዱ; ፍቅር ለተራቡም; ፍቅር ለጠገቡም ይሁን)

ሚያዚያ 7, 2001 ዓ.ም

2 comments:

Blog Archive