Sunday, January 23, 2011

ሲዘምር አየነው

የሚጠፋ መስሎት እንደ ጉም የሚተን
ያገር ፍቅር በኖ ሕዝብ የሚበታተን
ቋንቋን ተገን አርጎ ሀገር ሲሸነሽን
ጭፍራ ሲያሰማራ
ወገን ሊያስፈራራ
ሰው ባገሩ እንዳይኮራ
ሀገሩን ረስቶ ዘሩን እንዲያወራ
ባንዲራ ሲቀየር
ለምን የሚለውም ሲጣል ወደ እስር
ዘዴ ቢቀያየር ...
በርሀብ በርዛት በኑሮ ቢረግጠው
ወይ ፍንክች...!
ወገን እንደሆነ ተመልሆ ያው ነው
ክልጂ እስከአዋቂ
ኢትዮጵያን ሲያስባት
ሲዘምር አየነው:: !!


ቶሮንቶ ጥር 2003

ባለፈው ሳምንት የተከበረውን የጥምቀት በዓል በኢንተርኔት ካየሁ በኍላ የተሰማኝን ስሜት ለማንጸባረቅ ነው::

2 comments:

  1. Einqan adrshe Dimetrose yesafkwein getm saywe betam nwe desyalin DANKE I am wosene tsfaye from Germany,WOLLO, hotte.

    ReplyDelete
  2. Enkuan abro aderesen Wosene! Thank you

    ReplyDelete

Blog Archive