Saturday, November 24, 2012

የአቡነ ጴጥሮስ መታሰቢያ ሃውልት የሚያለማውስ?!

የዳግማዊ ምንሊክ አና የአቡነ ጴጥሮስ መታሰቢያ ሃውልቶችን ከስፍራቸው ለማንሳት ዝግጂቱ አንደተጠናቀቀ ስሰማ አሁን በስልጣን ላይ ያለው የህወሃት ቡድን በትክክልም የ”መለስን ራዕይ”ለማስፈጸም ደፋ ቀና አያለ አንደሆነ ተረዳሁኝ። ከዚህ በፊት በሌላ ፅሁፍ አንደገለጽኩት የ”መለስ  ራዕይ” የሚባል ነገር አንደሌለ እና የመለስ አየተባለ ለመሸጥ የሚሞክረው “ራዕይ” በትክክል የህወሃት ለመሆኑ አመላክቻለሁ። ጣሊያን ኢትዮጵያን ሲወር የነበረው የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ “ሃገሪቱን አሰለጥናለሁ” የሚል ነበር። አስቡት የኢትዮጵያ ስልጣኔ ጉዳይ ወዝውዞት ከጣልያን ሃገር ድረስ ጦር ሰብቆ ሲመጣ። አቡነ ጴጥሮስ በግፍ ሃውልታቸው የቆመበት ቦታ ላይ የተገደሉትም ዛሬ ህወሃት በሚጠቀመው ቋንቋ ሲመነዘር “ጸረ-ልማት” ናቸው በሚል ነበር።  


ሲጀመር “ልማት” የሚለው 'ዲስኩር' ከጥርጣሬ ይልቅ የህዝብን አመኔታ አንዲገዛ ማድረግ ያስፈልጋል። መረጃ በማፈን፣ ውዢንብር አንዲነግስ በማድረግ ደሞ የህዝብን ትኩረት ለጊዜው በማስቀየር ሌላ የፓለቲካ ጥፋት ከበስከጀርባ መስራት ይቻል አንደሁ አንጂ የሕዝብን አምነት መግዛት አይቻልም። በዚሁ ሃውልት ጉዳይ አንኳን የሚወራው ዜና የተደበላለቀ ነው። መጀመሪያ ይፈርሳሉ የሚል መረጃ ተለቀቀ። ህዝቡ ሲጯጯህ ደሞ “የለም አይፈርሱም” የአቡነ ጴጥሮስ ሃውልት ብቻ ነው ለጊዜው በባለሙያዎች “በክብር” ከቦታው የሚነሳው። ተመልሶም በባለሙያዎች በክብር የነበረበት ቦታ “በክብር” ይቀመጣል” የሚል መረጃ ተለቀቀ። የኋለኛውን መረጃ የምድር ባቡር "ባለስልጣን" (መሆኑ ነው) የተናገረው ተባለ።  የባለስልጣኑን ቃል አንደወረደ ማመን ከተሞክሮ አንጻር ስህተት  ሊሆን ይችላል። ማን ይሆን? ከየት ይሆን ብሎ -ለማወቅ ያህል- መጠየቁ ዘመኑ ከፈጠረው ፖለቲካ አስተሳሰብ ሳይሆን ካለው ነባራዊ የፓለቲካ የሃይል ሚዛን አና አሰላለፍ ነው መታየት ያለበት።  በ “ልማት” ስም መታሰቢያ ሀውልቱን በባለሙያ “በክብር ከማስነሳት” ይልቅ ሃውልቱ በማይነካበት ሁኔታ ባለሙያዎች መስራት የተፈለገውን ግንባታ አንዲሰሩ ስለመቻላቸው ወይንም ስላለመቻልቸው ስለመሞከሩ አና ስላለመሞከሩ የምናውቀው ነገር የለም። የራሳችንን ግምት ግን አንወስዳለን -የአቡነ ጴጥሮስ መታሰቢያ “ለህወሃት ምኑ ነው?” የሚል ጥያቄ ግምት ውስጥ በማስገባት። የህወህትን ተፈጥሮ አና ባህሪ ግምት ውስጥ በማስገባት!

 “ልማት”ን የአስከፊ ጥፋት መጠቅለያ ‘ዲስኩር’  እያደረጉ (አንደጣሊያኖቹ) ዝርዝር መረጃ ሲታፈን አና ነገሮች ከህዝብ ጋር ያለምክክር ሲደረጉ ጥርጣሬ ፣ሁከት፣አና ተቃውሞ አንደሚነሳ መዘንጋት ምን ማለት አንደሆነ አይገባኝም። ዛሬ ወታደራዊ ጉልበት ስላለ አና  የፖለቲካ መዘውር በሃይል ስለተያዘ ብቻም  ህዝቡ አሉኝ የሚላቸውን ከቅርስንትም ያለፈ ትርጉም አና ዋጋ ያላቸውን ታሪካዊም ፣መንፈሳዊም ማህበራዊም ሃብቶቹን አንደፈለጉ መነካካት አሁን ያለውን ትውልድ አና ህዝብ ኢትዮጵያዊ ስነ ልቦና በማድማት የሚያልቅ ጉዳይ አይደለም። የአለመረጋጋትን መሰረት አየጣሉ አንደመሄድም ነው። ተቃውሞው በሌላ መልኩ በሌላ ጊዜ  ሲከሰት  እንዳሁኑ በመጯጯህ አና በህዘን የሚያልቅ ጉዳይ ላይሆን ይችላል። ከ”ብሶት ተወለድኩ” የሚል ቡድን ብሶት ሊወልድ የሚችለውን ነገር መዘንጋት የለበትም።  የትውልዱ ማህበራዊ አስተሳሰብ  አና የሃገር ፍቅር ከጥቅም ውጪ ተደርጎአል፤ ስጋት የሚፈጥር ተቃውሞ ሊፈጠር አይችልም( “መቶ አመት አንገዛለን” አንደሚባለው”) የሚመስለው አስተሳሰብ ምናልባት ከትውልዱም የበለጠ የሚናገረው ስለገዢው ቡድን ትምክህትና አላዋቂነት ሊሆን ይችላል። በውጭም በውስጥም ያለውን የጥፋት ትስስር (nexus)ገብቶት አንደ አቡነ ጴጥሮስ ለሃገር ለመሞት የተዘጋጀ ትውልድ ቢነሳስ?  

ሕዝቡ “አለማለሁ” የሚለውን ቡድን የሚጠራጠረው ባህሪውን ስለሚይውቅ ብቻ አይደለም።  አንዳንድ “ልማት” የሚባሉ ፕሮጀክቶች በእርግጥም የልማት መሆናቸው አጠራጣሪ ስለሆነም ነው። ገዢውም ፓርቲ ለማወናበድም ዝም ለማለትም የሚምክረው የኢትዮጵያን ሕዝብ ስለሚያውቀው ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ከመሬት ተነስቶ አይጠራጠርም፤ተሞክሮውን ተመርኩዞ አንጂ!  የበፊት የበፊቱን አንኳን ትተን የቅርቡን የጥርጣሬ ምንጭ ለማስታወስ ያህል - የአፍሪካ የውሃ ማማ ናት በምትባለው ፤ ሰፊ የቆዳ ስፋት አላቸው ከሚባሉ የአፍሪካ ሃገሮች በምትመደበው ሃገራችን ውሃ አና መሬት የጠፋ ይመስል የስኳር ልማት ዋልድባ ላይ እተክላለሁ ተባለ። በጎን ደሞ ሃገሪቱ ያልተጠቀመችበት እጂግ በጣም ሰፊ መሬት አላት አየተባለ  ለውጭ ዜጎች ንጥቂያ አንጂ ሽያጭ አይመስልም በሚባል ዋጋ ሰፋፊ የእርሻ መሬቶችን አጥተናል። “ልማቱ” በትክክል የህወህት አጂ ብቻ ይሁን ወይንም የውጭ ሃይሎች አጂ ይኑርበት እስካሁን ድረስ የገባኝ ነገር የለም። በትክክል የማውቀው ነገር ቢኖር ግን ዋልድባ ድረስ የተሄደው የኢትዮጵይውያንን እምነት ለመዝረፍም አንጂ ለልማት  ጉዳይ  ብቻ አንዳልሆነ ከማንም የሚያገናዝብ ኢትዮጵያዊ አንደማይሰወር ነው።

የአቡነ ጴጥሮስ መታስቢያ በ “ክብር” የሚነሳበት ዓላማ በትክክል ልማት ከሆነ ሃውልቱ የሚያስተጋባው መልዕክት በራሱ ልማትም ለልማትም አስፈላጊ የሆነ መሰረታዊ ነገር አንደሆነ ማወቅ ያስፈልጋል። ሃውልቱ ካረፈበት ኩርማን መሬት ይልቅ ሃውልቱ የሚያስተጋባው መልዕክት ዘላቂነት ላለው የልማት ተሰሳሽነት አስፈላጊ ነው።  ልማት ለማጣደፍ የሃገር ፍቅር ያስፈልጋል። የዜጎችን ስብዕና አና ህሊና ማልማት ለልማት አንደ መሰረትም አንደ ቅድመ ሁኔታም መታየት አለበት። በስልጣን መባለጉ፣ በሙስና መዝቀጡ፣ የሃገር ጥቅም አሳልፎ መስጠቱ ፣ ሀገርን ለበላየ ሰቦች ጥሎ ወደ ሰው ሃገር ተሰዶ በሰው ሃገር መደላደሉ ሁሉ የሚመጡት ልማት ካላየው -ካልለማ- ስብዕና ነው። የራስን ዜጋ በሆነ ባልሆነው መጨፍጨፍ አና የመሳሰሉት ችግሮች መነሻቸው ያለማ ህሊና አና የሃገር ፍቅር አለመኖር ነው። ሃገሩን የሚውድ ዜጋ ሃገሩን የሚያገለግልበት ዕድል ሲያገኝ ሃገሩን አይዘርፍም። አያዘርፍምም። ህውልቱ  የሚያነበው አና የሚያዳምጠው  የመንግስት አክል ባይኖርም  የሚናገረው አነዚህን የሃገር ጠንቅ የሆኑ ማህበራዊ አና ፓለቲካዊ ተውሳኮች በመቃወም ነው፤ ለሃገር ጥቅም እስከሞት ድረስ በጽናት መቆም እንደሚያስፈልግ ነው። እንዴት “ባለ ራዕይ” የሚያመልክ ፓርቲ አና መንግስት ይሄን ማየት ተሳነው?

የአቡነ ጴጥሮስ ሃውልት መታሰቢያ  የጠንካራ ስብዕና ፣ የሃገር ፍቅር፣ የቁርጠኝነት አና የነጻነት ተምሳሌትነትን ነው ጧትና ማታ የሚያስተጋባው። በአስቸጋሪ ዘመን በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ አውነትን አንቆ ለእውነት ስለተሰዋ ክቡር ኢትዮጵያዊ ነው የሚናገረው። የአቡነ ጴጥሮስ የመንፈስ ጽናት ፤ መልዕክት አና መስዋዕትነት  የትግል ስንቅ ሆኗቸው ፋሺስትነትን በጽናት ታግለው ስለሞቱም ኢትዮጵያውያን የሚያስታውሰን መታሰቢያም ነው። ጎበዝ ኢትዮጵያ አኮ በፋሽስት ጦርነት አንድ ሚሊዮን የሚደርሱ ዜጎቾን አጥታለች። ስልሳ ሺ ታጋዮች ለትግራይ ተሰውላት ተብሎ ትግራይ ላይ ሃውልት የሚሰራ ቡድን በኢትዮጵያውን ሃውልት ለምን ይቀለዳል??  በቅርቡ የተሰራው የአባ ጳውሎስ ሃውልትስ ሃይማኖታዊ አይደለም ይፍረስ ሲባል አይፈርሲም ሲባል አልነበረ አንዴ? ምነው አቡነ ጴጥሮስ መታሰቢያ ላይ ተነቃ?! የአቡነ ጴጥሮስ መታሰቢያ “ለህወሃት ምኑ ነው?” ነዋ ነገሩ!  የአቡነ ጴጥሮስ ሃውልት ህወህት የተዋጋውን ኢትዮጵያዊነት ጧትና ማታ የሚያስተጋባ ነዝናዣቸው ነዋ!

የገዢው ቡድን በተለይም የህወህት ጽንፈኛ ደጋፊዎች የሚመስሉኝን ሰዎች (አንዳንዶቹ በብዕር ስም የሚጽፉ የአመራር አባላትም ይመስሉኛል) በዎብሳይቶች ላይ የሚጽፉአቸውን ጽሁፎች እከታተላለሁ። በዋነኛነት ከማነባቸው ውስጥ የሳይበር ኢትዮጵያን የፓለቲካ አምድ( click here  )አንዱ ነው። በኦፊሲየል ሲነገር የማይሰማውን የህወሃትን የፓለቲካ እሳቤ -በተለይም  ከትምክህትና የበላይነት ስለ ልቦና ግንባታ ጋር የተያያዙትን ህሳቦች ቡዙ ሳይነካኩ (አንዳንዴ ምንም ሳይነካኩም) አንደወረደ የሚያቀርቡ ግለሰቦች አይጠፉም።

አንደወረዱ የሚቀርቡትን ትቼ ትንሽ አየተነካኩ አንዳንዴ የስነ-ጽሁፍም ገጽታ እየተሰጣቸው የሚሰነዘሩ ሃሳቦችን ለአብነት አቀርባለሁ። አንደዚህ አይነት ሃሳቦችን ያንጸባርቃሉ ያልኳቸውን ጽሁፎች ለማየት በቅንፍ ውስጥ ያለውን ማጣቀሻ ይጫኑት( click here) ። ሃሳቡ የህወሃት ለመሆኑ ሁነኛ ማስረጃ ይሆናል ብየ ከማስበው ነገር እንዲህ ያለውን ጽሁፍ ብዙ ጊዜ የሚያሞካሿቸው (በዚያው መድረክ ላይ ማለቴ ነው) ህወሃት ባደረገው የትጥቅ ትግል ተሳትፈናል የሚሉ ስልጣን ከያዙ በኋላም ተምረው  በዲፕሎማሲ ስራ ላይ (ካያያዛቸው ይመስላል) የተመደቡ ይገኙበታል። ጉዳዩን አዚህ ያነሳሁብትም ምክንያት ህወሃት የሚከተላቸውን “የልማት” ይሁን ሌሎች የኢኮኖሚ ፓሊሲዎች  ዓላማቸው ህወሃት የበላይነት ስነ-ልቦን መገንባት አና የበላይነቱን ያስጠበቀበትን የስልጣን ተዋረድ ጠብቆ ለማቆየት የሚያስችለው ከመሆን ውጪ ሌላ ሊሆኑ አንደማይችሉ ለማመላከት ነው። አንዲህ አይነቶቹን ፓሊሲውች ህወሃት በቀጥታ የሚያስትላልፋቸው አይደሉም ማለት ህወህት የውሳኔው አድራጊ አና ፈጣሪ አይደለም ማለትም አይደለም (በነገራችን ላይ የህወህት አመራር ‘ሜንተሮችን’ አንማን ነበሩ? ናቸው?)።

ቅጥ ባጣ የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ እና የነጻው ፕሬስ ላይ የዘመተው ህወሃት መራሽ መንግስት ከዚሁ ጎን ለጎን በስፋት የተያያዘው ነገር የህዝብን ስነ-ልቦና የሚዘርፍበት ፣ ማህበራዊ አስተሳሰባችን ርባና ቢስ የሚያደርግበት ዘመቻ ነው (ለአስተሳሰቦቹ ሃውልት የተሰራላቸው አንገበዋቸው የኖሩ አና አንግበዋቸው የሞቱ ኢትዮጵያውያንን በመዘከር አንደሆነ አንዳይረሳ)። ማህብራዊ ስነ-ልቦና የሚዘረፍብት ምክንያት በዘራፊነት አና በግፍ ላይ የተመሰረተ የስልጣን ተዋረድ የማይቀርለትን ተቃውሞ በመገንዘብ  የተቃውሞውን ምንጭ አና ለስልጣን የበላይነቱ ችግር ይፈጥሩብኛል የሚላቸውን ጉዳዮች ከምንጫቸው ለማድረቅ የሚደረግ ጥረት አካል ሊሆን አንደሚችል አገምታለሁ።

የመሃል ሃገሩን ታሪካዊውን - ዓለም ጭምር ያወቀውን የነጻነት ትግል የሚያስታውሱ መታሰቢያዎችን በ “ልማት” ሰበብ  “መልስን በክብር አንደነበረ አናደርገዋለን” አየተባለ እየሰወርን በነበረው የርስ በርስ ጦርነት  “ተሰው” የሚባሉ የህወሃትን ታጋዮች የሚያስታውስ መታሰቢያ ትግራይ ላይ ለቱሪስት ማስጎብኘት  አና “በክልሉ” የሚያድጉ ህጻናትን ጭምር በዚህ መልክ ማነጹ አሁንም ትምክህት ክተሞላበት የፓለቲካ ስራ  ውጪ በዋነኛነት ከ”ልማት”ጋር የተያያዘ ነው ለማለት ያስቸግራል።  የሆነስ ሆነና ትግራይ ላይ ያለው ሃውልት ስለ ርስበርስ ጦርነቱ ሙሉ ገጽታ ይሰጣል? ለትግራይ ህጻናት ከ”ትግራዋይነት” እኩል ኢትዮጵያዊነት ስሜት አንዲፈጥሩ ያግዛል? የመሃል ሃገሩስ ታዳጊ ወጣት በራሱ አንኳን አነሳሺነት (መንግስት አንደማያደርገው አርግጠኛ ስለሆነኩ ነው) የሃገሩን ታሪክ አንዲጠይቅ የሚያስታውሰው መታሰቢያ አንዳያይ የሚደረግበት ምክንያት ስልታዊ የስነ ልቦና ዘረፋ ካልሆነ በስተቀር ምን ሊሆን ይችላል??

ህወህት የአርበኛውን የአቡነ ጴጥሮስን መታሰቢያ ህውልት አነሳለሁ በሚልበት ሰዓት ጣሊያኖቹ በኢትዮጵያ ብዙ እልቂት ላደረሰው የጦር መኮንናቸው (ግራዚያኒ) የመታሰቢያ ሃውልት ሊያቆሙ ነው። የህወህት መራሹ መንግስት ድርጊት ሳይታሰብ በአጋጣሚ የተደረገ ነው ? ምናልባትም የአማካሪ  ሃሳብም ያለበት ድርጊት ሳይሆንአይቀርም(ከላይ nexus ያልኩበትም የጥርጣሬ መሰረት ይሄው ነው)። የህዝብ ስነ-ልቦና ዘረፋ የመጨረሻው ደረጃ መሆኑ ነው። ይሄ ጉዳይ በቸልታ የታለፈ አንደሆነ አንድ ሰው ገስግሶ ዓይናችንን ሊያጠፋው ወደዓይናችን ሲጠጋ አይቶ አንዳላይ  አንደመሆን ነው። በድርጊቱ ቀጥሎበት ዓይናችን ከተዛቀ የሚደርሰው ነገር ከአካል ጉዳትኝነት  የከፋ ይሆናል።

የአቡነ ጴጥሮስ ሃውልት ሃይማኖታዊ የሆነ  አና የነፍጠኞች ነው ተብሎ የሚታሰበው( በህወሃቶች ዘንድ) የኦርቶዶክስ ሃይማኖት የሃይማኖት ቅርስ አይደለም። ክርስቲያን ላልሆነውም ኢትዮጵያዊም ቅርስ ነው። ታሪኩ የሃይማኖት ሳይሆን የነጻነት ትግል ታሪክ ነው።  ስለሆነም አሁን ባለው ነብራዊ ሁኔታ በተሻለ ሁኔታ ተደራጂተው እየታገሉ ያሉ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችም አንደ ኢትዮጵያዊነታቸው በጽናት ሊቃወሙት አና ሊያወግዙት  የሚገባ ድርጊት ነው።

የነጻነትን ትርጉም አየጠየቀ “ሊበራሊዝምን” ከእምነት በማይተናነስ መልኩ ተቀብሎ  ስለ ውጭ ሰዎች የነጻነት እሳቤ አና ትግል የሚነግሩን የፖለቲካ ሰዎች (“አደፍርሶች”) ፤ የአቡነ  ጴጥሮስ አይነት ክቡር ዜጋ  ስለ ነጻነት በተግባር የከፈለውን መስዋዕትነት የመነጋገሪያ ርዕስ አድርገው ቢያወሩን ኖሮ ዛሬ አንዲህ አይነት ነገር ሲሰማ የሚሰማው ቁጣ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል በሆነ። የነ አባ ጳውሎስ ሃውልት ተጎልቶ የአቡነ ጴጥሮስ ሃውልት በ”ክብር ከቦታው ይነሳል” አየተባለ ሲላገጥ ከመስማት የበለጠ ውርደት ለዚህ ትውልድ መቸም አይመጣም።


Wednesday, November 21, 2012

Not religious. It’s a political movement. own it!


So goes the saying: “if it looks like a duck and walks like a duck, it’s a duck.” What if it does not look like an eagle but it really is an eagle, seriously? Despite its peaceful and somewhat slow paced nature, what the Ethiopian Muslims are undertaking looks like revolution. Defiance and determination are crucially important revolutionary qualities, and there is no dearth of them in the undertakings of the Ethiopian Muslims. A peaceful, sustained and determined defiance of the TPLF led regime political intervention in religion. It’s a revolution in progress.

Yes, unlike most other revolutions in history, Ethiopian Muslims movement is free of spontaneous emotional actions. For instance, their march to Kaliti, the famous and infamous prison place in the outskirts of Addis Ababa, this week did not end up like the storming of Bastille –which was an important event in the famous French Revolution. Nevertheless, moderation did not overshadow the purpose it was intended for- which was visiting their arrested leaders. When hundreds of thousands of people march to prison to visit incarcerated leaders, it is not a social act. It is a political act. The way it unfolds itself is political. Its message is political too. In the process, it is shaping, I believe, consciousness in how to transform peaceful struggle into a revolutionary act.

Erstwhile strategies of domesticating and/or repressing peaceful demands are not working this time around and failed to outsmart the insight, bravery, subtlety and determination of the movement. What usually happens is that whenever there is peaceful struggle with a demand for justice or pursuit of political rights in a political way, TPLF led government swings to its habit of putting leaders of the movement behind bars apart from launching brutal atrocities, and then demands that caused the movement end up being relegated to demands of securing the release of leaders behind bars. In fact, that is not just it. Intensifying negative propaganda campaign, thanks to media monopoly of the government, putting activism for a cause in a bad light, framing it for “legal” attack and outright repression are norms for the governing TPLF dominated government. Movements in the past experienced all these entanglements and in most cases fell victim to it.

What distinguishes Ethiopian Muslim movement from all the previous movements is that it endured all the negative propaganda and atrocious attacks (attacks in Gerba ,Degan and Dessie comes to mind) and it is marching forward, as it should like a revolution. Of course, the movement has already achieved something extraordinary: it disempowered ethnic ideology and unified people from all language speaking groups and the bond looks strong. Far from being suspicious about the movement, on grounds of alleged “Islamist agenda” driven by expatriate extremists – as government did try to project it, majority of the non-Muslim Ethiopians are relishing it and are sympathetic about it. Apparently, the piquant glance emanates partly from the history of Islam in Ethiopia and partly from the strong social bond between Ethiopian Muslims and Ethiopian Christians. Clearly, many Ethiopians are convinced that the Ethiopian Muslims are not in the business of selling out their country and non-Muslim Ethiopians for expatriate Muslims - whatever their agenda is. Yet, it has to be admitted that there is still a significant number that is not at ease with and even suspicious about the movement.

We have to be clear about the demands. Although, the movement is being undertaken by Ethiopian Muslims, there is really nothing that is purely religious or even religious about the movement. What they are resisting (in fact now it is in a stage of defiance, which is revolutionary) is political intervention from TPLF dominated government which manifested itself in three forms: that government should not appoint, clandestinely, its own personnel to their Islamic council, that government should not orchestrate (in any form) infiltration of strange Islamic teachings (they refer to it- Al-Ahbash) to their congregation and that government should not interfere in the business of running their Islamic school.

These demands are, as Mesfin Negash expounded a few months back, related to, and in a fundamental way, assertion of (or defending) constitutional rights and there is nothing apolitical about it. When constitution and assertion of rights are involved (it does not matter whether the issues are related to religion or not), and when these assertion is pursued outside of the courts in a very political way due to the very political nature of the “justice system”, the movement is clearly not religious. In that case, the process through which the assertion of rights are pursued and what the process results in are inevitably political.

And this is what makes the Ethiopian Muslims movement more of a “rights movement” rather than a religious one (as it is related to assertion of constitutional rights outside of the court) and this is why non-Muslim Ethiopians need to take up the issue aggressively and own it instead of disowning the movement on illusory religious grounds and on grounds of manufactured suspicion. Even if we assume that the alleged unEthiopian root of the movement is true and the “agenda” it seeks to promote is something “radical”- in which case it would be political again, disowning the movement does not render service to skepticism that is lingering among some Ethiopians. Yet, I want to be clear on this matter: as a person who grew up where religious difference did not matter in social interaction, where religious difference did not cause conflict, and where religious difference did not even matter in marriage (not because people were less pious about their faiths but because social harmony was so strong), there is no reason to buy the pessimist propaganda of “hidden agenda” and disown the political movement simply because Ethiopian Muslims took the initiative to be serious about their rights and happened to be harbingers of impending “rights revolution” (not to be confused with the US “rights revolution” in the 1960’s). The movement is not religious. It’s political movement.

A revolution is in the making. And it is in the interest of all Ethiopians to own the movement and even more Ethopianize it. Those of us who are simply relishing the movement need to do something more significant and meaningful. Those who are skeptical about the movement need to kill their skepticism and be able to see the very political nature of the movement, have a share, be part of it and own it. Opposition leaders, especially young leaders in the opposition, need to approach the movement and the leaders and discuss in how to make the “rights revolution” possible. I understand this is a risky business for the opposition. Yet, the moment is a moment of defiance. Seize it.

Thursday, November 15, 2012

Tell it like it is: Chauvinism, in its worst form, is the real danger


The late Meles Zenawi made, it seems, more appearance in international print and electronic media and became a preferred topic for think thanks and researchers alike after his demise than he did in his 21 years of rule. Substances in discussions range from retrospective analysis of his personality to his contribution, from his “influential” presence in international politics to impending instability, which, for some, is inevitable.

Emerging accounts in most cases nearly tally, except differences in wording and presentations, with the official government account which paints Meles simply as exceptionally mystic (political and social) in the entire history of the country – even in the continent. Most that we read are rosy portrayals: “selfless”, “insightful leadership” and “influential in the world stage.” I have no doubt in my mind that most of the leadership of his circle of ex-guerrilla friends do not mean it.
The motive of mystification, so to speak, has a lot to do with crafting political legitimacy to help maintain their uneasy hold on power. Meles Zenawi is now like an ideology unto himself: he is like the “Chairman Mao” of Ethiopia. I get it, I hope any one would, why his friends in the leadership position are in the business of reformation and transformation of the image of the late Zenawi. What I don’t get is the sort of confirmation from international actors and politicians in the international stage. Among others, Susan Rice is exceptionally annoying in that. Some organizations seem to send similar message, subtly.

Recent analysis,actually they call it briefings, (here after the paper), from a UK based “non-governmental organization” that “aim to provide high level analysis of rapidly emerging and unexpected global events and their impact on global development policy and practice” is subtly rosy: “...without the steadying hand of a practised and seasoned global player, Ethiopia’s presence and capacity for global influence may well have diminished.” My question is: “how do we measure influence?” Could the size of financial aid from “The International Community” be an indicator as to how influential a leader is in the world stage? If so, how is Zenawi different from Nouri Almaliki of Iraq and/or Hamid Karazi of Afghanistan, or from the former Egyptian president Hosni Mubarek? The more international organizations are trying to transform an image of Meles Zenawi ( an image that never existed), the more clues they give about their real nature and where they stand on issues like justice, democracy and corruption, among other things. What would emerging young critical voices in Ethiopia, who are a living witnesses of the atrocities authorized by Zenawi, think about these organizations?

That is not just it. The paper discussed findings or observations rather in the areas of “politics of transition”, “geopolitics” and the economy as it relates to “development” of Ethiopia. Besides numerous inaccuracies of descriptions and statements throughout the paper, it ignores matters which would otherwise have been essential for the discussion in the creation of stability and democratic ambiance in the post Meles Ethiopia. I'll not do justice if I try to address them all. I’ll just focus on selected issues which I think are even more crucially important.

First of all, it seems that an implied assumption is made that political instability is not a thing of Meles Zenawi's administration. If that is the case, the truth is entirely different. May be how we view political stability/instability played into the making of the assumption. Whatever the case is, it is not disputable that Meles Zenawi presided over one of the most brutal regimes in Africa. And to transform Meles’ image in total disregard to his brutal aspect which caused agonies to thousands and thousands of people amounts to condoning injustice and human rights violation.

Among other evidences, records in the hands of reputable international human rights organizations like the Human Rights Watch and Amnesty International vindicate repeated mass killings in the capital, south central, south eastern and south western parts of the country among others. Civil society is virtually non-existent. The attack on free press was and is exceptionally brutal to the extent that vocal critics of the political system could simply be implicated in trumped up charges of “terrorism” and the best journalists in the country are thrown to prison. The justice system is simply serving a distinct form of totalitarian regime –one that espoused ethnic chauvinism as an ideology. Opposition leaders are thrown to jail with manufactured false allegations. Opposition parties are pushed to the point of irrelevance not just because of organizational weakness and lack of vision, as indicated in the paper, but because “legal”, political, security and economic muscle of the government is being flexed regularly to make the idea of peaceful and democratic political opposition nearly impossible and creation of a single party state, like China, possible. When institutions are non-functional and repression is considered as a norm and political virtue, they do not tell stories of political stability. It is more like political instability. Regular invitation and attendance at the G-20 and other international gatherings should not blind analysts from seeing the fact that political instability was part and parcel of 21 years of Meles rule, and in fact he engineered it.

In regards to political transition, while the paper captured, rightly, the insignificance of “political transition”, and uselessness of assumption of the premiership position by Hailemariam Dessalegne, it tends to employ a reductionist approach on the explanations of it. And what that does is that it camouflages the real sources of political instability. The paper simply tries to explain the obvious that TPLF (Tigray People’s Liberation Front) is more powerful –militarily, economically and in terms of controlling security apparatus – than other members of the ruling coalition. Had the problem been that simple, not that it really is simple from the point of view of democratization process but relatively speaking, anticipated challenges would have been less worrisome. They need to tell it like it is: The problem is manifested aspiration to chauvinism and ethnic supremacy and that is the true ideology of TPLF. Yes, this is one the most ridiculed subjects in Ethiopian comedy but needs to be a point of political discussion, not just a matter to laugh at. Not just it represents a malaise for the democratization process (by the way there is no aspiration for democratization on the part of the government. The trend is Sinification ), it may bring about total chaos as well.

Look at the political transition itself. It generated tension within the ruling coalition not because, apparently, other members of the coalition have qualms, political doubt or bitter feelings about the nominated premier but because of the ideology of TPLF. Leaked information suggests that there was acrimonious conflict within TPLF over the idea of prime minister from other members of the coalition. There was meetings after meetings before confirming Hailemariam Desalege to the position of premiership. With all its legal ambiguities, chapter 8 article 75, No. 1. section “B” of the constitution stipulates that the Deputy Premier “Act on behalf of the Prime Minister in his absence.” Hailemariam Desalege was the Deputy Primer when Meles passed away, and of course death is an irreversible absence. It took months after the death of Meles for Hailemariam Desalege to be confirmed as Prime Minister. The hurdle standing on the way of Hailemariam Dessalege was mainly TPLF’s ethnic chauvinism ideology. In the swearing ceremony, the incoming prime minister vowed religiously, allegiance and unquestionable commitment to the visions of Meles Zenawi. Even more laughable, after taking over the position, he was not living in state house and had to live in a government owned apartment and drive (well someone did it for him) to work only because the Widow refused vacate state house. What is the vision of Meles Zenawi after all? Anything that is not in line with the interest of TPLF supremacy agenda cannot be a vision.

The real political issue which is either ignored or overlooked but that which beefs up the likelihood of political instability is aspiration to chauvinism and ethnic supremacy of the “mightiest” political entity in the coalition which in fact seems to have tendency to take form of extremism at some point in the future if legitimate questions of proportional power allocation and putting legal limits to its power are pursued passionately.

Albeit not known or ignored by the donor community, “international community” and key state actors in the international forum, ethnic chauvinism was significant component, both as a means and an end, in Meles Zenawi’s power politics in the country. Ample evidence could be drawn from the policy agenda of TPLF and the power structure in the military and security apparatus. In a recent interview with a radio station owned by TPLF, Meles’ widow, Azeb Mesfin, unveiled that Zenawi had already designed a plan to exceptionally industrialize his ethnic base region (Tigray) which is already exceptionally industrialized, in the Ethiopian context. And his ethnic party has everything it takes to materialise the plan.

Apart from tight ethnic based control over military and security apparatus, the wealthiest and the not so wealthiest economic structures owned by TPLF are pursued as means to maintain dominance. TPLF runs the biggest business empire, perhaps in the entire continent. There are many reasons as to why people in Ethiopia shrug off to the alleged story of economic growth -the least of which is not exclusion from the benefit of economic growth. Most of the beneficiaries of the growth are TPLF party members, its former guerrilla fighters and their families but we do not see that in the growth data. What makes this political and military dominance born affluence in Ethiopia different from that of Chinese leadership is the fact that the one that exists in Ethiopia is essentially a making of ethnic chauvinism ideology and a means to maintain ethnic supremacy. And this is what makes it dangerous and this is what is missing from discussions.

Geopolitical analysis is problematic too, to say the least. Among other things, it foresees that “Mohammed Morsi will adopt a more Islamist approach; aligning interests in Sudan, Somalia and Egypt with Muslim communities in Ethiopia.There are many in the Ethiopian establishment who fear a Muslim Brotherhood-led Egypt is capable of exploiting simmering tensions between Ethiopia’s government and its large Muslim population (officially about 30 per cent of the population).” Whether Mursi has such a plan or not is not something I can tell. What I can tell is that “many” do not fear “Mursi agenda.” Ethiopian Muslims are simply in the business of pursuing their constitutional rights to loud their voice in opposition to government interference in their religious affairs which in fact has support from non-Muslim Ethiopians. There is no reasonable ground to believe that Ethiopian Muslim would exchange their fellow non- Muslim Ethiopians to the “Islamic approach” of Mursi in the region, if there is one. The Christian-Muslim relation in Ethiopia is exceptionally unique and is based on recognition and respect. I do not dare to say no extremist element could be found among Ethiopian Muslims. But I can tell that if they exist they could not influence the majority.

Let us get it again,the real danger, if not arrested in time, that would trigger perhaps an irreversible political instability is TPLF’s aspiration and pursuit of ethnic chauvinism and ethnic supremacy agenda, and its determination to maintain political supremacy at the expense of coalition members or drag the country into political instability of exceptional magnitude.


Thursday, November 1, 2012

ለ"ወጣት ሴት የመሆን ጣጣ" የተሰጠ አስተያየት

"ወጣት ሴት የመሆን ጣጣ" በሚል ርዕስ ሶልያና ሽመልስ አና ማህሌት ፋንታሁን ላስነበቡን ግሩም መጣጥፍ የተሰጠ መልስ ነው። ልክ ጽሁፉን አንብቤ አንደጨረስኩ የተሰማኝን ሳልነካካው አንደወረደ ያነበብኩበት ፌስ ቡክ ገጽ ላይ የሰጠሁትን አስተያየት ነው ትንሽ ማስተካከያ አድርጌ አዚህ ላይ አምጥቼ የለጠፍኩት። ሌላ ጊዜ የራሴንም የነሱንም ጽሁፍ ደግሜ አይቼ የምጨምረውም የምቀንሰውም ነገር ሊኖር ይችላል። ለዛሬ ግን አዛው ላይ የሰጠሁትን ሃሳብ ላካፍል።

መሰረታዊ አና ውይይት የሚያስፈልገው ጉዳይ ወደ አደባባይ ይዛችሁ በመውጣታቸው አድናቆቴን አንገልጻለሁ። በጹሁፉ የተዳሰሱ ጉዳዮች ሰፋ ያለ ውይይትን የሚጋብዙ አንደሆኑ አንድና ሁለት የለውም። ከሴት ልጂ ወይንም ከወንድ ልጂ የህይወት ፍልስፍና አና የአኗኗር ዘየ ጋር ብቻ የተያየዘ ሳይሆን በማህበራዊ ፋይዳውም --ህብረተሰብን ወደ ፊት ለማራመድ ወይ ወደ ኋላ ለመጎተት ሊያሳድር የሚችለውን ተጽዕኖ ግምት ውስጥ በማስገባት መወያያት ያስፈልጋል። ሰፋ አድርገን ስናይ አንደኔ አንደኔ የጽሁፉ ጭብጥ በባህል አና ማህበራዊ አስተሳሰብ ባንድ በኩል አና ፤ በሌላ በኩል ተተኪ የሚባለው ትውልድ ራሱ ከሚፈጥረውም ይሁን ከሌሎች ማህበረሰቦች በፊልም ይሁን በሌሎች የመገኛና ዘዴዎች በሚያገኛቸው አስተሳሰቦች መካከል የሚነሳ ቅራኔን ወይ አለመጣጣምን በወጣት ሴቶች አንጻር የሚያሳየን ጽሁፍ ነው ባይ ነኝ። ጉዳዮ ወደ ርዕዮተ-ዓለማዊ እይታ አይወስድም አይባልም- ሊወስድ ይችላል። በነገራችን ላይ ብሎግ የጀመርኩ ሰሞን ላነሳቸው ከሞከርኳቸው ርዕሶች አንዱ ይሄ ነበር-ምንም አንኳን አዚህ ስላለው ማህበረሰብ ላይ ያተኮረ ቢሆንም። አንድ ጊዜ አንደ ክርክር ምሽት ቢጤም ለማዘጋጀት ሞክረን ነበር በጉዳዮ ላይ።




የዘረዘራችኋቸው ችግሮች መልካቸው ለየት ቢልም አዚህ ሰልጥኗል የሚባለው ማህበረሰብም ውስጥ አሉ። ከሌላ ከሌላው የዕድሜ አና የትዳር ነገር አዚህም አነጋጋሪ ጉዳይ ነው። በሰሜን አሜሪካ በትዳር መረበሽ ምክንያት "ሲንግል ፋሚሊ" የሚሉት ነገር ይበዛል። ዕድሜያቸው ከሰላሳ በላይ ሆኖ ያለትዳር የሚኖሩ ነጠላዎችም ቁጥራቸው የዋዛ አይደለም። በነገራችን ላይ አዚህ ሃገር አንደመጣሁ "quick divorce" የሚል በየቦታው የተለጠፈ ማስታወቂያ ግራ ያጋባኝ ነበር። የጠበቆች ዋነኛ ገበያ ከሚባሉት ውስጥ አንዱ ሰው ማፋታት መሆኑ ነው አንግዲህ። በሌላውም ጉዳይ ይሄ ማህበረሰብ "ሊቲጋንት" የሚባል አይነት ማህበረሰብ ነው። መካሰስ የሚወድ ይመስላል። የ"ህግ የበላይነት" ከመኖሩ ጋር የተያያዘ ነው ወይንስ በሌላ ምክንያት የሚለው "ሶጂዎሎጂካል" ጥናት አና ምርምር የሚያስፈልገው ይመስለኛል። የተጻፉ ብዙ ነገሮች ሊኖሩ አንደሚችሉ ግን እገምታለሁ።

የፍቺ ቁጥር መብዛቱ የገረመኝን ያህል ከዛም የከፋ ነገር አለ። ከሁሉም የማልረሳው ነብሰጡር የነበረች ባለቤቱን ባሰቃቂ ሁኔታ የገደለም አለ-አዎ አዚ የ"ባህል ተፅዕኖ" በሌለበት ሰልጥኖአል በሚባለው ዓለም። ጉዳዮ ግን የጋዜጣው የፊት ገጽ ዜና ("ፍሮንም ፔጂ ኒውስ") አንደሚሉት አንኳን ለመሆን አልበቃም። አንግዳ ወይም ተከስቶ የማያውቅ ነገር ባለውመሆኑ ይሆን ከርዕሰ ዜናነት የተቀነሰው? ውስጠኛው ገጽ ላይ አንዳነበብኩት ነው የማስታውሰው። 'ቶሮንቶ ስታር' ወይንም 'ቶሮንቶ ሰን' ጋዜጣ ላይ። (አሁንም ጉዳዮ ባይያያዝም ትላንት አንግሊዝ ሃገር ሁለት ልጆቾን ያረደች አናት ሰምተናል።)

አዚህም ያለው የኢትዮጵያውያን ማህበረሰብም አንደሌላው ማህበረሰብ በጾታ ግንኙነትም ሆነ በትዳር ላይ የሚከሰቱ ውጥንቅጦች ተጠቂ ነው። በማደግ ላይ ባሉ ሃገሮች ነጠላ ቤተሰብ (ልጂን ያለ አባት ወይ ያለ አናት የሚያሳድጉ ) አየበዙ አንደሆነ የሚጠቁም ንባብ አንዳነበብኩም አስታውሳለሁ። በተለይ መንግስታዊ ባልሆኑ የውጭ ድርጂቶች ተቀጥረው የሚሰሩ አናቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ልጆቻቸውን ያላባት ማሳደግ አየተለመደ መጥቶአል የሚል ነገርም ይሰማል። የሚሰሩበት የውጭ ድርጂት ውስጥ አብረዋቸው ከሚሰሯቸው የውጭ ሃገር ሰዎች ( ብዙ ጊዜ አለቆቻቸው ናቸው) አና የንባብ ተጽዕኖ ነው ወይንስ ተወልደው ያደጉበት ማህበረሰብ "የባህል ጫና" ነው ችግሩ የሚለው በርግጥ ጥናት አና ትንታኔ የሚጠይቅ ነገር ነው። ወይንስ ሁለቱም?

ከሌላ ከሌላው ግን የባህልን ተጽዕኖ ስናነሳ በግንኙነት ላይ ችግር የሚፈጥረው ባህላዊ አስተሳሰብ ብቻ ነው ብሎ ማለት የነገሩን ክብደት ማሳነስም ፤ የችግሮቹን ምንጮች በሙሉ አለማየትንም ያስከትላል። ከዚህ ከጽሁፋቸሁ የተረዳሁት ከባህል ጋር በተያያዘ የእኛ ባህል የአብዛኞቹ ችግሮች ፈጣሪ አንደሆነ ተደርጎ የታየ ይመስላል። ለምሳሌ ከታች ኮት ያደረኩኣቸው ግልጽ አይደሉም-

"...በዚህ ላይ የማኅበረሰቡ ግልጽነት ያጣ ጫና እና ማስፈራሪያ ለአንዲት ወጣት ሴት የመረጃ ምንጯ ጓደኞችዋ ብቻ፣ ትክክል የሚሆነውም ብዙዎቹ ጓደኞችዋ ያደረጉት ነገር ይሆናል፡፡ ..."

".... እነዚህ ጠንካራ እሴቶች በመካከለኛ የወጣትነት ዘመን ላይ ሲደረስ በከፍተኛ ተግዳሮቶች እና በተለመዱ ትዳርን የመጨረሻ የሴት ልጅ ስኬት አድርጎ በሚያይ ማኅበረሰባዊ እሴቶች ውስጥ ይዋጣሉ፡፡ ..."

"...እነዚህ ጠንካራ እሴቶች በመካከለኛ የወጣትነት ዘመን ላይ ሲደረስ በከፍተኛ ተግዳሮቶች እና በተለመዱ ትዳርን የመጨረሻ የሴት ልጅ ስኬት አድርጎ በሚያይ ማኅበረሰባዊ እሴቶች ውስጥ ይዋጣሉ፡፡ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ በሀገራችን ሴት ልጅ በተማረች እና በበቃች ቁጥር ስኬታማ የቤተሰብ እና የትዳር ሕይወት የመመስረት እድሏ ይቀንሳል፡፡... "

የአናንተን ጽሁፍ ተከትሎ ከተሰጠው አስተያየት አንዱ በማህበረሰባችን "ሴት ልጂ ምንም ቫልዮ" አንደሌላት የሚያስመስል ነገርም ተሰንዝሮአል። ታሪካችንም ማህበራዊ ግንኙነታችንም ሙሉ በሙሉ አንደዛ የሚያሳይ አመስለኝም። ተወዳጂ ሚስት፣ተወዳጂ እህት፣ተወዳጂ አናት አና ተወዳጂ ልጂም ጭምር ከሴትነት ውጭ ካየናቸው ሚዛናዊነትን ልናጣ አንችላለን። የሴቶች ተሳትፎንም በተመለከተ በምዕራቡ ዓለም በሚታወቀው መጠን እና ልክ ባይሆንም (በነገራችን ላይ የነሱም ታርክ የግማሽ ምዕት ዓመት ታሪክ ነው) ለሃገራችን ታሪክ አንግዳ ነገር አይደለም። በአኛ ማህበረሰብ ውስጥ "የሴት ወንድ ናት!" የክብር ልብስ ነው። ሴትነቱንም ወንድነቱንም አስተባብረው የያዙ ነበሩ በታሪክም። ርግጥ ነው በ"ፌሚኒስት ፐርስፔክቲቭ" ይሄ ራሱ የሚተች ነገር ሊሆን ይችላል። ትንሽ ወጣ ማለት አንዳይሆንብኝ አንጂ "ሚሊታንት" የሚባለው አይነት "ፌሚኒዝም" ጭራሽ አናትነትን ሁሉ የማይቀበል ነው። ተፈጥሮኣዊነቱን አየሞገተ ልጆች መፈጠር ያለባቸው ከሁለቱም የዘር ፍሬ ተወስዶ በ "ቴስት ቲዮብ" ነው ብሎ አስከማመን አና ለዛም አስከመታገል የሚደርሱ አሉ። ባደኩበትም ማህበረሰብ ውስጥ ቁጥራቸው ባይበዛም የሴት ወንድ የሚባሉ ሴቶችን አውቃለሁ። ከአመራርም ጋር በተያያዘ የዛሬን አያድርገው አና ብርቱካንን አይተናል...የኦብኮ አመራር አባል የነበረችውን አልማዝ አይተናል( ህወሃቶች በጣም ግፍ ፈጸሙባት የሚባል ነገር ብንሰማም)። ስድስት ኪሎ በነበርኩበትም ኪዜ ከወንዶች አመራሮች ጋር አኩል በትጋት ይሰሩ የነበሩ ልጆችን አይተናል። አና ራዕይ ያለው እና ፖለቲካ አንባቢ ላይ የባህል ተፅዕኖ አለ የሚለው ትንሽ ማብራሪያ ያስፈልገዋል ይመስለኛል።

የፖለቲካ አስተሳሰብ ከህብረተሰቡ እምነት አና ባህል ጋር በሚጋጭ ጊዜ የሚፈጠር ተቃውሞ ከሴትነት ጋር ተደርቦ መታየት ያለበት አይመስለኝም። በግሌ ለመናገር ያህል ባባህላዊ አንጻር ለሴቶች የሚገባውን ክብር መስጠት ያስደስተኛል። ልክ ለእናቴ አና ለእህቴ አንደምሰጠው ያለ። ለሴትነት የሚሰጠው አክብሮት በባህላችን መሰረትም አለው። ከ"ፌሚኒዝም" አንጻር ነገሩ ሲነሳ ግን ነገሩን በፖለቲካ መነጸር አንጂ በባህል አንጻር አላየውም። አንደ አሰተሳሰብ አውቅና ከምሰጠው በስተቀር አንዲህ ያለ አስተሳሰብ ለሚያቀነቅኑ የሃገሬ ልጆች የምሰጠው አውነተኛ ክብር የለኝም። የማላከብረው ራስን ከመሆን ጋር የተያያዘ ጉዳይ ስለማይመስለኝ (ሰለማይመስለኝ!) ነው። ራስ የሚለው ጉዳይ አከራካሪ ሊሆን ይችላል። ከፊልም አና መስል ነገሮች ለሌላ ጉዳይ የተፈጠሩ የካፒታሊስት የፖለቲካ አስተሳሰቦችን እየያዙ "አኔ ይሄ ነኝ" ማህበራዊ አና ባህላዊ አክብሮት ይሰጠው ማለት ያስቸግራል። "እመቤቴ ማርያም" አያለ የሚያምን ማህበረስብ ለሴት አክብሮት የለውም ማለት ድፍን ያለ ነገር አንዳይሆን!

ትንሽ የተነዛበት ፕሮፓጋንዳ ጠንከር ባለ ሚዛናዊነት ስላልተመረመረ አንጂ የአኛ ባህል የትዳርን ተፈጥሮ አና ባህሪ ተረድቶ በ "አንተ ትብስ አንቺ ትብሺ" ዘየ አንዲያዝ የሚገፋፋ አና የማይናቅም ስኬት ያሳየ ነው። ትዳር አና የፍቅር ግንኙነት ውስጥ የህግ አና የፖለቲካ አስተሳሰብ መቀላቀል አና በዛ መመዘን ተፈጥሮውን መንሳት ይመስለኛል። የተቃራኒ ጾታ ግንኙነትም ሆነ ትዳር ስለ መብት አይደለም። አንደዛ ከሆነ ፓለቲካ አና ህግ ሆኖ ቁጭ ይላል። ስለ ፍቅር ነው። የችግሮቹን ምንጮች ስንመረምር ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል ለማለት ነው።

"ዘመናዊነት"ስ ራሱ የፈጠረው ችግር የለም? ድሮ ኋላ ቀርቶአል ይባል በነበረው ማህበረሰባችን ውስጥ የልጁቹን አናት በ25 ጥይት ደብድቦ የሚገድል ሰው መኖሩን በአጂጉ አጠረጠራለሁ። ከዚህ የወንጀል ድርጊት በፊት የተበላሸ ነገር አለ። አገሌ ነው አገሌ ነው ማለት ጣጣ ውስጥ ሳይገባ በተለያየ መልክ ከውጪ የተቀበልነው ባህል የራሱ የሆነ ድርሻ የለውም ለማለት እቸገራለሁ። በማያቸው የአማርኛ ፊልሞች ላይ የማስተውለው የወንድ አና የሴት ኮንቨርሴሽን አንኳን መመነጫጨቅ ሲንጸባረቅበት ነው የማየው። መመነጫጨቅ ከሌለበትም ልክ አንደውጪው በህዝብ ፊት ያልተለመደ መሳሳም ይስተዋልበታል። ፈጽሞ የባህላችን አይመስልም። አንደዛም አየሆነ አሁንም አንደ ጭራቅ እየታየ ያለው ባህላችን ነው። ባላችን ፍቅር ያልነገሰበት አና ለሴት ልጂ አክብሮት የማይሰጥበት ነበር ማለት ስሜታዊነት አልፍ ሲል ደሞ አላዋቂነት ሊሆን ይችላል። የነገስታቱ የፍቅር ታሪክ ራሱ የሚለው ነገር አለ። የቤተሰብ አና የትዳር ዋጋ ክተጋጋለ ወሲባዊ ስሜት ባነሰ ሁኔት አየታየ የመጣ ይመስላል። ይሄ ከባህላችን ጋር ግንኙነት አለው ማለት ትንሽ ፍርደ ገምድልነት ሊሆን ይችላል። ገበያ ያላችው ጹሁፎችንም ጸሃፍቶችንም እያየን ነው። በወሲብ ዙሪያ አደሚያጠነጥኑ አያየን ነው። አየሰማን ነው። የሙዚቃ ስራዎችም ይዘት አና መልዐክቶቻቸው ስለ ዘመኑ ግንኙነት የሚሉት ነገር አላቸው። ወሲብ ወሲብ ወሲብ።

ትዳር አንደስኬታማነት መለኪያ ቢታይ ችግር የለውም ባይ ነኝ። ነገር ግና ያለጾታ ምርጫ ለወንዱም በሴቱም ነው መለኪያ መሆን ያለበት። ያላገባ ሴት ስኬታማ ካልሆነ ያላገባ ወንድም አንደዛው። በትዳር ውስጥ ሊያጋጥም የሚችልም አለመግባባትም የትዳርን አላስፈላጊነት የሚያመላክት ሊሆን አይችልም። እድሜውን መለኪያ ጨብጦ ሌላ ቁምነገር ሳይሰራ የሚያልፍን ወንድ ማህበረሰቡ አንደችግር ቢያየው የአስተሳሰባችን መሰረቱ( አስካሁን ባለው) ማህበራዊ ስለሆነ አና የግለሰቡ ችግር ብቻ ተደርጎ ስለማይታይ መሆኑ ግምት ውስጥ ሊገባ ይገባል። በተመሳሳይ ሁኔታ ሴቶች ይሄን ነገር ሲያድርጉ ቢታዮ አንደችግር ከመታየት አያመልጥም። በእኛ ባህል። ከማግባት አና ካለማግባት ብቻም ጋር የተያያዘ ሳይሆን ስይገባ የሚሰራውም ነገር የሚወስነው ይመስለኛል። ያላገባች ሴት ስትመነኩስ አንደ ችግር ሊታይ አይችልም። ያላገባም ወንድ ሲመነኩስ አንደችግር ሊታይ አይችልም። የሚሸረሽረው አና የሚፈትነው ማህበራዊ አስተሳሰብ ስለማይኖር። በምንኩስናውም ውስጥ የሚገኝ ማህበራዊ ጥቅም ስለሚኖር። ለትዳር የሚሰጠው ክብር አና ክብደትም ከግለሰቦቹ ባለፈ ከሚያበረከተው ሃገራዊ ድርሻም በመነጨ ነው። ቤተሰብ የህብረተሰብ ቀጣይነት የሚረጋገጥበት አንደኛው መንገድ አይደለ አንዴ? ቤተሰብ ከሌለ የማህበረሰብ መስረቱ ምን ሊሆን ይችላል? የሴተኛ አዳሪነትንት የሚያስተቸው አና ነውር ያድረገው አንደኛው ጉዳይ ሃይማኖታዊ እይታ አና በማይነገድበት ነገር ላይ በመነገዱ ብቻ አይደለም። በቤተሰብ ምስረታ ላይ የራሱም የሆነ አፍራሽ ተጽዕኖ ስላለውም ጭምር ይመስለኛል።

ሰሞኑን ባነበብኩት አደፍርስ ዛሬ "ፊሚኒስት" ሊባሉ የሚችሉ አይነት ሴትን አይቻለሁ- ወይዘሮ አካላትን! (ገጽ 36 አካባቢ ይመስለኛል) አምስት ያህል ባል አግብተው ከአምስቱም አምስት ልጂ ወልደው ከአምስቱም የተፋቱ ናቸው። ግድ የለሽ ናቸው --- ይሄ ነው የሚባል የባሎቻቸው ትዝታ አስከማይኖራቸው ድረስ! ማቴሪያሊስትም ነበሩ ---የዛኑ ያህል ደሞ ማህበረሰባቸውን ወደው አንደማህበረሰባቸውም የኖሩ ናቸው በሌላ ገጽታው። "አደፍርስ" ላይ ከተነሱት ጠቃሚ ማህበራዊ ጉዳዮች አንዱ የግንኙነት አና የትዳር ጉዳይ ነው። የትዳርን መሰረት ምንነት በዘመናዊ ትምህርት የተገኘ እውቀትን ክማህበራዊ አስተሳሰብ አና ባህል ጋር አዋዶ ሳያጣላቸው ጥሩ አድርጎ አስቀምጦታል። ቁንጂና የሚባለውንም ነገር ልቅም አድርጎ ስሎታል! አዛ ላይ ያሉት አንስቶች ቆንጆቆች ነበሩ። ቁንጂናቸው ግን ከኮስሞቲክስ ስና መሰል ጉዳዮች ጋር ያልተያያዙ ነበሩ። አንዳንዴ የአኛን ማሀበረስብ በሌላ ማህበረስብ ከመስፈራችን በፊት መጽሃፉ ላይ አንደሚንጸባረቀው ያለንን አና የሌለንን በጥሞና ብናጤናቸው ጥሩ ይመስለኛል። ያለ በለዚያ ብዙ አደፍርሶች አሉ። ከውጪ አየተጫነበን ያለው ነገር በራሱ አደፍርስ ነው። ለማንኛውም ከዚህም ሰፋ ያለ መስል ስለሚያስፈልግ ጊዜ አንደፈቀደ አመለስበት ይሆናል። በድጋሚ ጂምሩ ግን ጥሩ ነው።

Blog Archive