Saturday, January 29, 2011

እስከመቼ?!

ተሸክሞ የብሶት ቁልል
ችጋርና ርሀብ ቤቱን ሰርቶ
ቁራሽ ምኞት ሆኖ አርፎ
በፈረቃ እየተበላ ስንቱ
በየቤቱ ራሱን ስቶ
ቁራሽ ፍለጋ ተከልቶ
ቀየውን መንደሩን ትቶ;
ከሁለት ያጣ እንዲሉ
ቁራሹም ጠፍቶ ላመሉ
ቀየውንም ቁራሹንም እየተራበ
ጉደኛ አሳዳሪ...
""ዕድገት"" አለ እያለ ከበሮ ደረበ::

"" ህዳሔ አለ ...ዕድገት አለ
አስፋልት ተነጠፈ
ጥርጊያ መንገድ ተደለደለ
ለዕድገት ተብሎ..
ለአረቡ; ለቻይናው; ለህንዱ መሬት ታደለ
ዕድገት አለ:: ""

እንዲህ አይነት ፌዝ እየሰማ
አበሽ ልቡ እየደማ
በረሀብ የሚፈጀው
ረሀብ እና ባርነት ያደረጀ 'ሚታገሰው
እስከመቼ ነው?!

የ""አትንኩኝ"" ባይነት መንፈስ
ነጻነት ባበቀለበት ምድር
ዛሬ "አትንኩኙን" ማን ቀጠፈው
ማን ቀላቀለበት ከአፈር::

ምነው አበሽ ዝምታ አበዛ አንገቱን ሰበረ
"'ከመናገር ደጃዝማቺነት ይቀራል"" ተረስቶ
ስለምን ለዘራፊ አሳዳሪ አቀረቀረ??

ኧረ እንደልማድህ አበሽ
ኑር እንደ አባት አደሩ
ችጋር; ባርነት ለሚደግስ
እስከመቼ እሺሩሩ??



ጥር 2003 ቶሮንቶ

No comments:

Post a Comment

Blog Archive