Friday, December 4, 2009

ውጪ ሀገር

ነገሩን ለማያቅ ውጪ የሚባለው ስሙ ቢያስደስትም
ውስጡ ለቄስ ይሁን እንደስሙ አይደለም
ብዙ ቢባልለት አኗሪ አንቀባሮ
የተወለወለ ቢያስመስል ብርሌ ገጽን አሳምሮ
ባይታይ ነው እንጂ ብዙው ከውስጥ ጠቁሮ
በደስታ ደህይቶ ይኖራል እሮሮ
አይ የውጭ አገር ኑሮ !!!

No comments:

Post a Comment

Blog Archive