Tuesday, May 29, 2012

ሀገር አቅኚ

ሸፍጥ በመልኩ ሸፍኖ
አሻሮ እምነት አሻሮ ባህል ከሌላ ዘግኖ
ወደ እናቱ ቆሎ የሚጠጋ
ከባዕድ አብሮ 'ሚዶልት
ሀገር ""በምክንያታዊነት "" የሚያባልት
ሀገር 'ሚያቀና አለ:: የልጂ ጠፍ ; የልጂ ሙት ::



Monday, May 28, 2012

እነማን ነበሩ??

(በቅድሚያ የአማርኛ ስርዐተ-ነጥቦችን ባግባቡ ጠብቄ ስላልጻፍኩ በትዕግስት እንድታነቡኝ እጠይቃለሁ:: የተፈጠሩ የአማርኛ ግድፈቶችም ካሉ ይቅርታ እጠይቃለሁ::) መልካም ንባብ!

በዚህ ዘመን አሉ ከሚባሉት የሙዚቃ ሰዎች ውስጥ ቴድሮስ ካሳሁንን በግንባር ቀደምነት የማስቀምጠው ቴድሮስ ባለው የድምጽ ቅላጼ እና በሚደርሳቸው የሚመስጡ ዜማዎች ብቻ አይደለም:: ግጥሙን ራሱ ስለሚጽፈውም ብቻ አይደለም:: ከዚህ ባለፈ በግጥሙ ውስጥ የሚንጸባረቁ መልዕክቶች እና ያላቸው ሀገራዊ ፋይዳ ነው ቴድሮስን ለየት የሚያደርጉት:: ያደገበትን ማህበረሰብ ወግ ባህል እና እምነት ከማንጸባረቅም በተጨማሪ ዘመን የወለዳቸውን የህዝብ ስነ-ልቦና መመሰቃቀል እና ችግር ተረድቶ በሙያው ችግሩን በመቅረፍ ረገድ የሚያበረክተው አስተዋጾ ቴድሮስን ከድምጻዊነትም ያስበልጠዋል:: የጥበብ ሰውን ሀገራዊ ፋይዳ የምንሰፍረው በዚሁ ይመስለኛል::

ህሊናውን ያለምንም ስጋት እና ጸጸት የሚሸጥ እየበዛ መምጣቱን ያስተዋለው ቴድሮስ (የማይሸጡ እና ለእምነት የሚሞቱ እንዳሉ አውቃለሁ!) "ዋሽቶ ከመኖር ...አንገት ከሚሰበር ባይበላስ ቢቀር'’ በሚለው ዘፈኑ ያደግንበትን ማህበረሰባዊ አስተሳሰብ ብቻ ሳይሆን ስለህሊና ክቡርነት አስታውሶናል:: መንፈሳዊ ህግን እና ማህበረሰባዊ አስተሳሰብን አስተሳስሮ የያዘ የሰው ልጂን ለእውነት እና ለፍትህ የሚያተጋ ማህበረሰባዊ ተልዕኮ ; ፋይዳ ብሄራዊ እና መንፈሳዊ ግዴታንም ነው ያስታወሰን:: ጽድቅስ ቢሆን የሚመጣው ከእምነት በተጨማሪ ከህሊና ንጽህና አይደለም እንዴ??በየትኛውም ዘመን እና ቦታ ለሚኖር ትውልድ እውነትም ከህሊና ንጹህነት በላይ ሰውን የከበረ የሚያደርግ ነገር ስለሌለ የሰው ልጂ ህሊናውን በጥቅም ሲቀይር የሚዘፈቅበትን የንዳማ አሮንቃ የሚያስታውስ ዘፈን ነው::
ከዜማ ዘመን ተሻጋሪነት ጋር በተያያዘ በዘመናችን ስለምናውቀው እና ስለምንመሰክርለት ቴድሮስ እንደመግቢያ አነሳሁ እንጂ አነሳሴ ስለ ቴዲ አፍሮ ለመጻፍ አልነበረም:: እንደሀገራችን አቆጣጠር በሰባዎቹ ውስጥ ከተቀነቀኑት ዘመን ይሻገራሉ ስለሚባሉ ( ዘመን የማይሽራቸው ) የሙዚቃ ስራዎች ውስጥ ---በነሙሉቀን መለሰ ; ማህሙድ አህመድ; ኩኩ ሰብስቤ እና ጥላሁን ገሰሰ ድንቅ የሙዚቃ ስራዎች ውስጥ የሌላ ሰው እንጂ እንዳለበት ሰሞኑን ባየሁት አንድ ኢንተርቪው ስለተረዳሁ እጂግ በጣም ስለገረመኝ ነው::

የዓለምፀሀይ ወዳጆን ታዋቂ ተዋናይነት እየሰማሁ ባድግም ከዚያ ባሻገር ድንቅ ገጣሚ እና ጸሀፊ ስለመሆኗ የማውቀው ነገር አልነበረም:: በአሜሪካ ራዲዮ የአማርኛ ቋንቋ ፕሮግራም በተለያየ ጊዜ እየቀረበች በተለያዮ ጉዳዮች ላይ ቃለ መጠየቅ እንደሚደረግላት አስተውያለሁ:: በቅርቡ ደሞ ስለ እናት እጂግ ግሩም የሆነ ግጥም አእንዳቀረበች አውቃለሁ:: ከዚያ ውጭ ዓለምፀሀይ ድንቅ ገጣሚ እና ጸሀፍት ስለመሆኗ ያወቅኩት ከዚህ ቃለ-መጠየቅ ነው::

ከታች ባለው የዓለምፀሀይ ቃለ-ምልልስ የምናውቀው ስለእሷ ብቻ አይደለም:: ካስተዋልን ሌሎች ብዙ ነገሮችን ማየት እንችላለን:: በዘመኑ የነበረውን ማህበራዊ ሁኔታ ; የወጣቱን ስነ ልቦና ; የነበረውን የፖለቲካ ተሳትፎ; በመምህራን እና ተማሪዎች መካከል የነበረው ግንኙነት; በከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ደረጃ እንኳን የነበረው ማህበረሰባዊ ሀላፊነትን የመወጣት ስሜት እና ትጋት; ወጣቶችን በመቅረጽ ረገድ የነበራቸው ተሳትፎ እና የትወና ጥበብ በሀገራችን መሰረት እና ፋይዳ እንዲኖረው ደፋ ቀና ስላሉ እና በውል ስላልተዝከሩ ሰዎች ትናገራለች::




በተለይ ትኩረቴን የሳበው ህይወታቸውን ለሀገር መስዋዕትነት በመክፈል እና በተለያየ ምክንያት ወላጆቻቸውን ያጡ ህጻናትን በአምባ ህጻናት ማሳደጊያ ማዕከል አስባስቦ በእንክብካቤ እና ፍፁም ኢትዮጵያዊ በሆነ ሁኔታ ቤተሰባዊ ፍቅር እየሰጡ ለማሳደግ የተደረገው ጥረት በእውነት ልብ ይነካል:: ጨካኝ በሚባለው በደርግ ዘመን እንኳን ይህን ማድረግ ተችሏል! እንዲህ ያለው ነገር ያለውን ማህበራዊ እና ሀገራዊ ፋይዳ ለመረዳት አሁን በህወሀት (TPLF) መንግስት የህግ እና የፖለቲካ ከለላ ሴት እህቶቻችን በገፍ ( ሰሞኑን ባለኝ ንባብ በወር እስከ 45, 000 ድረስ) በባርነት መልክ ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚላኩበትን ሁኔታ እና ህወሀት ቤተሰቦቻቸውን ያጡ ኢትዮጵያውያንን በማደጎ እያወጡ ለባዕዳን በመስጠት ረገድ ከቻይና ቀጥሎ ሁለተኛው መንግስት እንደሆነ ከተረዳሁ እና የኢትዮጵያ ህጻናት ለማደጎ እየቀረቡ ለህወሀት እና ለስርዐቱ ደጋፊዎች የውጭ ምንዛሬ ምንጭ የሆኑበትን ሁኔታ ስናስብ ያኔ ለተሰራው ስራ ዋጋ እንድንሰጥ ያደርገናል:: ዓለምፀሀይ በህጻናት አምባ ህጻናት ህይወት የነበራትንም ተጽዕኖ ለማወቅ ችያለሁ:: ኮሌጂ እያለሁ ከህጻናት አምባ የመጣ አንድ ጓደኛ ነበረኝ በጣም አስቂኝ እና የቲያትር ዝንባሌም የነበረው ነው:: ምክንያቱ የገባኝ ግን አሁን ነው::

ከዚያ ውጪ ወደ ዓለምፀሀይ ሁለገብ ሰውነት ስመለስ የፖለቲካ ተሳትፎ አንዱ ገጽታ ነበር:: እንደገባኝ ድሮ ፖለቲካ ህወሀት እንደሚያደርገው መጀመሪያ ትውልድን አደገኛ ቦዘኔ ብሎ በሽብር አንቀጥቅጦ ሲያበቃ መለስ ብሎ ደሞ የእኛ ደጋፊ ከሆንክ የደህንነት ዋስትና እና እንዳቅምህም መንደላቀቂያ ታገኛለህ ተብለው ስለተስፈራሩ የሚገቡበት አልነበረም:: ፖለቲካ የእምነት ነገር ነበር:: ደርግን የወደደ ከደርግ ኢሀፓን የወደደ ( በህቡዕም ቢሆን) እንደየእምነቱ የሚገባበት ነበር:: የደህንነት ዋስትና ለማግኘት ደርግ ጋር የገቡ አይኖሩም ለማለት አይቻል ይሆናል:: ያኔ የነበረው ስርዐት የለየለት የቅጥረኛ መንግስት ቢሆን ኖሮ እያወቁ ይገቡ ነበር ለማለት ግን ያስቸግራል:: ፖለቲካ የፍርፋሪ መሰብሰቢያ አልነበረም:: (በነገራችን ላይ ስለ ህወሀት ጨካኝነት እና ሀገር አጥፊነት ስናስብ ልንዘነጋው የማይገባ ጉዳይ የሰው ልጂን በዚህ ዘመን ልክ እንደባሪያ የፖለቲካ ባሪያ አድርጎ በፍርፋሪ መግዛት ራሱን የቻለ - እንደውም ለመጭውም ትውልድ ጭርም የሚተርፍ ቶርቸር እንደሆነ ሊሰመርበት ይገባል:: ማዕከላዊ እያስገቡ የሰውን አካል የሚገርፉት ነገር ወንጀል ቢሆንም አካል ያገግማል:: ጉልበት አለኝ ብሎ ዘጎች በገዛ በሀገራቸው የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዳይሆኑ በማድረግ ካስራቡ በኍላ ህሊናቸውን በፍርፋሪ መግዛት ከአካል ግርፋት የበለጠ ኢ-ሰብአዊነት እንደሆነ የተዘነጋ ይመስለኛል::)

ከፖለቲካው ተሳትፎ ውጪ ደሞ ዓለምፀሀይ ከላይ ለጠቃወስኳቸው ሀገራችን ባፈራቻቸው ድንቅ ድምጻውያስ ስራ ውስጥ አሻራዋን ትታለች:: ሙሉቀን መለሰን ስናስን ""ቁመትሽ ሎጋ ነው"" ""እንደኔው አእምሮ"" ""መውደዴን ወደድኩት"" ልንረሳ አንችልም:: እነዚህ ግጥሞች የዓለምፀሀይ ወዳጆ እንደነበሩ ያወኩት ከዚህ ኢንተርቪው በኍላ ነው:: የጥላሁን ገሰሰን ""ኢትዮጵያ"" የሚለው ዘመን የማይሽረው ዜማ (ህወሀት ኢትዮጵያዊነትን ማጥፋት እስካልተሳካለት ድረስ ማለቴ ነው) ግጥም የዓለምፀሀይ ወዳጆ ነው:: የኩኩ ማራኪ ""ደኔ በለው"" ዜማ ግጥም የዓለምፀሀይ ወዳጆ ነው:: ሌሎችም ያልጠቀስኳቸው ብዙ ዜማዎች አሉ::


በኢንተርቪው ላይ ዓለምፀሀይ የጥበብ ሰው ዋጋ በገንዘብ እንደማይተመን የተናገረችው ነገር ልብ ሊባል ይገባዋል:: የጥበብ ሰው ዋጋው የህዝብ ፍቅር ነው:: ከሊስትሮ ጀምሮ እስክ እውቁ የህክምና ሰው ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ! ለዓለምፀሀይ የተንጸባረቀው ፍቅር ዓለምጸሀይ በተሰጦዋ በሙያ አንጻር እና በሌላም መልኩ ለሀገሯ ቁም ነገር ያለው ስራ ስለ ስራች ይመስለኛል:: ዓለምፀሀይ ለምን እንዲህ ሆነች ነው ጥያቄው?? ዓለምፀሀይ ተሰጦዋ በተፈጥሮ ያገኘችው ቢሆንም ተሰጥኦዋን ተረድተው ያበረታቷት እና ወደ ውጪ ያወጡላት መምህራኖቿ እንደሆኑ ተናግራለች:: በተሰጦዋ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው ስራ እንድትሰራ ተልዕኮ የሰጣት ሀላፊነት የጫነባት ግን አስተዳደጓ የኢትዮጵያዊነትን ፋይዳ እና ለኢትዮጵያዊነት የተከፈለውን መስዋዕትነት በማወቋ የኢትዮጵያውያን ባህል እና እምነት ለኢትዮጵያውያኖች ያለውን ፋይዳ እና ትርጉም በየዕለቱ እየኖረችው ስላደገች ነው:: ተሰጦውን ለንግድ ተግባር እና ለሀብት ማካበቻነት መጠቀም እና ተሰጦን ለሀገር እና ለህዝብ መታመኛነት ማዋል ከፍተኛ ልዮነት አላቸው:: ልዮነቱን ማወቅ እና የበለጠ የህይወት ርካታ እና በኢትዮጵያውያን ዘንድ የክብር ልብስ የሚያጎናጽፈውን ለይቶ ለማወቅ በትክክል ማሰብ እና የህይወትን ትርጉም መረዳት ይጠይቃል:: ይሄ ደሞ ከእውቀትም የሚመጣ ነው::

ባካበቱት ሀብት ከሚታወቁ ሰዎች ይልቅ በተሰጥኧቸው የህዝብን ክብር እና ሞገስ ያተረፉ የበለጠ ዘላለማዊ ናቸው:: ብዙ ጊዜ ""ህይወት አጪር"" ናት የሚል አባባል እሰማና ከዚህ በኍላ የሚከተለው ዓረፍተ ነገር ""ተደሰት ጨፍር"" አይነት ነገር ይቀናዋል:: በዚህ አስተሳሰብ ምክንያት አንዳንዶች ሳይራቡም ህሊናም መሸጥ ጣጣ ውስጥ የሚገቡት ከዚህ ትርጉም አልባ ከሆነ አስተሳሰብ በመነጨም ነው:: ህይወት አጭር ከሆነች ከመጨፈር እና ጭፈራ ባቆመ ማግስት በሚጠፋ ደስታ ያለፈ ፋይዳ ሊኖራት ይገባል:: ህይወት አጭር ከሆነች ለእምነት እና ለእውነት ልንኖርባት ይገባል:: ህይወት አጭር ከሆነች ከትውልድ ትውልድ በዘመን ውስጥ በጥሩ መንፈስ ሊተላለፍ የሚችል ቁምነገር የሚሰራባት መሆን አለባት::

ዛሬ ብዙዎቹ አርቲስቶች ንቃተ ህሊናቸው በደንብ ያልዳበረ ንባብ እና እውቀት የሌላቸው ከመሆናቸው የተነሳ የህወሀት መንግስት እየሰራ ያለውን የማስመሰያ ስራዎች በአግባቡ ባለመረዳት ; የህወሀትን አጭበርባሪ ባህሪ እና ጸረ-ኢትዮጵያ ባህሪ ጠንቅቆ ባለማወቅ የተነሳ የስርዐቱ ደቀ መዛሙርት በመሆን ራሳቸውም ደንቁረው ህዝብም ሊያደነቁሩ እየሞከሩ ነው:: እንዳይማል አልፎ አልፎ አንዳንድ አርቲስቶች አሉ:: እኔ እንደገባን እንደሜሮን ጌትነት ያሉት አርቲስቶች እንደ ዓለምፀሀይ የመሆን እድል ያላቸው ይመስላል:: ሌሎችም አንዳንድ አይጠፉም:: እንደነሰራዊት ፍቅሬ ያለ የስዳይ ዱባም አለ!
ከዓለምፀሀይ ጋር የተደረገው ቃለ-መጠየቅ በተለይ ወጣት ኢትዮጵያውያን ሊያዮት የሚገባ ነው እላለሁ!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!






Tuesday, May 1, 2012

Sunday, April 29, 2012

“የሀበሻ ጀብዱ”

ከተፃፈበት የቸክ ቋንቋ ርዕስ Habešská Odyssea “የሀበሻ ጀብዱ” በሚል የተተረጎመውን መጽሀፍ በተመስጦ አነበብኩት:: መጽሀፉን የጻፉት ቸኮዝሎቫኪያዊው (በድሮው) ብዙ ጊዜ እንደተለመደው “ታሪክን እና ማህበረሰብን እናጠናለን” በሚል ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት መዛግብትን በማስተርጎም እና ቃለ-መጠየቅ በማድረግ በየሚያሳትሟቸው መጻህፍቶቻቸው ስለ ኢትዮጵያ እንደሚዘባርቁት ሳይሆን ከዚህ በተለየ ምክንያት ፈታኝ በሆነ ሰዐት ኢትዮጵያ ተገኝተው በብዙ የጦር ውሎዎች እና ሌሎች ሁነቶች በአካል ተግኝተው ያዮትን ነው የጻፉት:: አልፎ አልፎ በአንዳንድ ጉዳዮች ላይ አስተያየት ከሚሰጡ በስተቀር ጸሀፊው ከትንተና እና ማብራሪያ ታቅበው የጦርነት ውሏቸውን እና ገጠመኖቻቸውን በጥሬ መረጃ መልክ አቅርበዋል:: ይሄ ማለት ለታሪክ ተመራማሪዎች በመረጃነት ለትንተናቸው እንደመነሻ የሚሆን እጂግ ጠቃሚ ስራ ነው ማለት ነው:: የታሪካዊ ምርምር አጻጻፍ ክህሎት የሌለውም ቢሆን ከታሪኩ ሊወስድ የሚችላቸው ጠቃሚ መረጃዎች አሉ::




ከኢትዮጵያዊነት እሴቶች ጋር በተያያዘ ሲንጸባረቅ የሚታይ ደግነት : የዋህነት: ፈሪሀ እግዚያብሄር እና እምነት : አልበገር ባይነት: እጂግ በጣም ጥልቅ የሆነ ከነብስ ጋር የተሳሰረ የሀገር ፍቅር: የአሸናፊነት ስነ ልቦና : ታዛዢነት : ታማኝነት : አንድነት: ከልክ ያለፈ ወኔ : ግፍና መከራ ችግር ቻይነት የመሳሰሉትን ስናይ በሌላ በኩል ደሞ ከነውር እና ከሀጢያት እኩል ይቆጠሩ የነበሩ ከኢትዮጵያዊነት እሴት ጋር አይን እና አፈር የሆኑ ነገሮችንም እናያለን:: ከክህደት እና ሀገር አሳልፎ ከመስጠትም በተጨማሪ ከጠላት ጎን ተሰልፎ በገንዘን ተቀጥሮ ኢትዮጵያን የወጋ አለ:: ስግብግብነት አለ:: ወራት ያስቆጠረ ረዢም መንገድ እና እንግልት ተቋቁሞ ህይወቱን ሊሰጥ ትግራይ መሬት የረገጠውን ከከምባታ ከሰላሌ ከሸዋ ከጎንደር እና ከሌላውም የመሀል ሀገር የመጣውን የኢትዮጵያን ሰራዊት ከጣሊያኖች ስንቅ እና ትጥቅ ድጋፍ ጠይቆ ተደራጂቶ የዘረፈ እና ኢትዮጵያን የወጋ ቡድንም አለ:: (ከታች ከነማጣቀሻ ገጹ በጨረፍታ እጠቁማለሁ:: )

የታየው ክህደት የሚያበሳጨውን ያህል ጸሀፊው ቅልጥ ባለ ጦር ሜዳ ላይ በባለ ጎራዴው የኢትዮጵያ ገበሬ እና እስካፍንጫው በታጠቀው የጣሊያን ሰራዊት መካከል በነበረው ግብ ግብ ባለጎራደው የኢትዮጵያ ገበሬ በደም ፍላት እየዘለለ የጣሊያኖቹን አንገት ሲመትር ያዮትን የጀግንነትና የወኔያምነትን ጥግ ያለ ምንም ቁትብነት ስዕላዊ በሆነ ሁኔታ ሲገልፁ የሚሰማ የንዝረት ስሜት አለ:: ለቁጥር የሚሰለቹትን ትተን ሀያ አመት የማይሞላው የአቢቹ ታሪክ ራሱ የሚገርም ነው:: በሀገራችን የሲኒማ ጥበብ ያደገ ቢሆን ኖሮ እንደ አቢቹ እና ደጃዝማች አበራ (የራስ ካሳ ልጂ) ያሉ ወጣቶች ከፈጸሙትም ጀብዱ ካሳዩት ወደር የሌለው መንፈሰ ጠንካራነት በተጨማሪ በማህበራዊ ግንኙነት አንፃር የነበራቸው ግንዛቤ አስተዋይነት እና የሀላፊነት ስሜት --- የጦር አውድማውን እና እንደ ወጣት ያሳዮትን ያመራር ብቃት የሚያንጸባርቅ ደህና ፊልም ተሰርቶበት ለትውልድ ጥሩ አስተማሪ ሊሆን ይችል ነበር::
በነዛ ጀግኖች ትውልድ እና በእኛ በእንዝህላሉ ትውልድ መካከል ያለውን ልዮነት ለመተንተን ሞከርኩ:: ባያረካኝም:: የድሮው ወጣት ወኔ አለው:: የሀገር ፍቅር አለው:: ፈሪሀ እግዚያብሄር አለው:: ምናልባት የባህል ወረራ ሰለባ ካለመሆኑ ጋር የተያያዘ ነገር ይሆናል:: አሁን በግልጽ እንደሚታየው ወይ ወኔ የለም:: ወይ የሀገር ፍቅር የለም:: ወይ እምነት የለም:: ወይ ሁሉም የለም:: እነዚህን ሁሉንም አንድ ሰው ላይ ማግኘት አስቸጋሪ ነው የሚሆነው:: የማህበረሰባዊ አስተሳሰብ እና ትኩረት ልዮነትም ይመስለኛል:: ከስነ-ጥበብ አቅም ከእኛ ቀደም ያሉት የሚያንጸባርቁት ፍጹም ሀገራዊ ስሜት እና ማህበረሰባዊ ፋይዳ ያላቸውን ነገሮች ነው:: ይሄን ለማስተዋል ቀደም ያሉትን የሙዚቃ እና የድርሰት ስራዎች ብቻ ማገላበጡ ይበቃል:: ስለ አርበኝነት ስለ ሀገር ፍቅር ኢትዮጵያውያን ስላደረጉት ደጋድሎ ይዘመር ነበር:: "እንኳንስ በህይወት እያለሁ በቁሜ ለሀገሬ ነጻነት ይዋደቃል አጽሜ"" የተቀነቀነው በ70ዎቹ አጋማሽ ወይ መጨረሻ ነበር:: የተደረገውን ተጋድሎ እየሰሙ ያደጉ ትውልዶች በመሆናቸው የሀገር ፍቅር ስሜት እና ለሀገር መጋደልን በባህሪ ስለወረሱ ይመስለኛል::

አሁን ዘመን ተቀይሯል::ገጣሚያን እና ጻሀፍት የሚያነሱት የሚጥሉት ነገር እንደምታዘበው የፍቅር አርበኝነት ነው":: የወጣቱ ተግባር "ማፍቀር ማፍቀር አሁንም ማፍቀር ነው"በሚል አይነት መንፈስ እንኳን አሁን እና ከአስራ አምስት አመት በፊት የነበሩ የልብ-ወለድ ድርሰቶች "የፍቅር አርበኝነትን" የሚያንጸባርቁ አይነት ነበሩ:: የ"ሀብታም ልጂ" የደሀን ልጂ ስታፈቅር ወይ ሲያፈቅር ወይ የሚወዳትን ልጂ ለማግኘት የተፈጠሩ መሰናክሎችን ሲያልፍ … "እምቡጥ ጽጌሬዳን ለምቅጠፍ እሾሁን ማለፍ ያስፈልጋል” አይነት ትረካ ያስነብቡናል ...." “ ውዴ አንቺኮ ማለት ለኔ ሁለ ነገሬ ነሽ”....”አንተ እኮ ማለት ማለት ‘ድቅ ድቅ ባለ ጨለማ ብርሀን ለመፈንጠቅ እንደምትወጣው ውብ ጨረቃ ነህ ...ህይወቴ ያላንተ ብርሀን አይኖረውም” ያስነብቡና እና መጨረሻ ላይ ገጸ-ባህሪ ጭምር ይገሉና የፍቅር አርበኝነቱም በሞት ተጠናቆ አሳዛኝ እንዲሆን ይደረጋል:: ጨለምተኝነት አና የአቸናፊነት ስነልቦና የማያውቀው ሆኖብኝ ቁጭ ይላል::የድሮዎቹ ወጣቶች የሚያነሱት የሚጥሉት (ሮማንቲሳይዝ የሚያደርጉት ሀገር እና ህዝብን ነው:: ) “አንቺ እኮ ማለት ለኔ” የሚሉት ኢትዮጵያን ነው:: አስተሳሰባቸው ርባና በሌለው ምክንያታዊነት የተበረዘ አልነበረም:: የህይወትን ትርጉም የሚያዮበት መነጸር ኢትዮጵያ ነበረች:: የፍቅር ህይወት የላቸውም ማለት አይደለም:: ለመለያየት ካለመፈለጋቸው የተነሳ ተያይዘው ጦር ግንባር የሚሄዱ ሁሉ ነበሩ:: የሚንቀለቀል የሀገር ፍቅር ስሜት በዛን ዘመን ከእድሜ ጋር እንኳን አብሮ የሚያረጂ አልነበረም:: የጦር ምክር ተደርጎ ለመዝመት ከተወሰነ በኍላ የኢትዮጵያ ገበሬ ወታደሮች በራስ ካሳ ፊት የገቡት ቃል ሁኔታውን የሚያመላክት ይመስላል:: በገጽ 50 ላይ እንዲህ ጽፎታል :-
"አንድ ቆፍጣና በራስ ካሳ የሜዳ ላይ ተንቀሳቃሽ ዙፋን ፊት ቀርቦ ጎራዴውን እያወናጨፈ 'በዚህ ጎራዴ አስራ አምስት አንበሶች ገድየበታልሁ: ሁለት እጥፍ ጣሊያንም እገላለሁ' እያለ ፎከረ:: ከማልረሳው ለመጥቀስ ያህል አንድ አዛውንት ጎራዴያቸውን እያወናጨፉ 'በዚህ ጎራዴ ከእምየ ምኒሊክ ጋር አስር ጣሊያን ገድያለሁ:: አሁንም መቶ እጥፍ ጣሊያን እገላለሁ" የሚለው ፉከራ አንዱ ነው:: ሌላው አንድ በግምት ሀያ አመት የማይሞላው ጎረምሳ ሲናገር "እኔ ወጣት ነኝ: ከዚህ በፊት ጀግንነቴንና ታማኝነቴን ለማሳየት እድል አልነበረኝም:: አሁን ግን ሀገሬን ሊወር የመጣን ጣሊያን እንደ ቆሎ አቆላዋለሁ:: አንዱንም አልምርም ሲል በስሜት ተናገር"" ገጽ 50- 51 [ የሀገር ፍቅር እና የአሸናፊነት ስነ-ልቦናው ከትንሽ እስከ ትልቅ ተመሳሳይ እንደነበረ የሚጠቁም ይመስለኛል]

ሴት ወንድ ሳይል የሚያጠቡ ጭምር እንደዘመቱ የሚያመላክትም መረጃ አለ:-
...በዚህ እንደሞላ ወንዝ እያጓራ በሚጓዝ ጦር ውስጥም እንደነገሩ ሸማ የተከናነቡና በጀርባቸው በቅርጫት ሙሉ የማብሰያ ቁሳቁሶች ያዘሉ ሴቶችም ነበሩ:: የሚጠባ ልጂም የተቸከሙ ታይተዋል..."ገጽ 72

በዘመናችን ያለውን ወኔ ቢስነት ከመመዘን በፊት በዚያን ዘመን የታየውን ከልክ ያለፈ ጀግንነት ምክንያት መጠየቅ ያስፈልጋል:: የዚህ የጀግንነት ሚስጥር ምን ነበር?? ምናልባት ብዙ ትንተና እና ጥናት የሚያስፈልገው ጉዳይ ሊሆን ይችላል:: ብዙ ምርምር የማይጠይቀው ነገር ግን የሀገር ፍቅር ለክብር እና ለነጻነት የሚሰጥ ዋጋ ከምንም በላይ ደሞ በፈጣሪ ላይ ያለ ጠንካራ እምነት ይመስለኛል:: ክርስቲያኑ ከልቡ ክርስቲያን ነው:: እስላሙም እንዲሁ ከልቡ እስላም ነው:: ስለ ነበረው የእምነት ጥንካሬ ያንጸባርቃሉ ያልኳቸውን ልጥቀስ:-

...በጦር ሜዳም ሳይቀር መጸለይይቻላቸው ዘንድ እያንዳንዱ ከፍ ከፍ ያለ ሹም ሳይቀር የራሱን ቄስ የራሱን ነብስ አባት ይዞ ነው ወደ ጦር ሜዳ የመጣው:: ቄሶችም ሆኑ ሼኮች የራሳቸውን የሆኑ ወታደሮች ያላቸው ከመሆኑም በላይ በጦር ግንባር ሜዳም ጠመንጃ ይዘው ይሳተፋሉ …
….በጸሎታቸውም ያገራቸውን ድንበር በማን አለብኝነት ደፍሮ የመጣን የጠላት ሰራዊት ከሀገራቸው ጠራርገው ያወጡ ዘንድ እግዚያብሄር ብርታቱን ሰጥቶ ይረዳቸው ዘንድ ሳይታክቱ በየምሽቷ ይለምናሉ: ይማጸናሉ:: ... ' ጦራችንን ሰብቀን ጎራዴያችንን መዝዘን ጠመንጃችንን አንስተን እናባርራቸዋለን::ገጽ 166-167 [በእግዚያብሄር/በአላህ ርዳታ መሆኑ ነው::]

እንዲህ ያለ የሀገር ፍቅር እምነት እና ጀግንነት በበቀለበት ምድር ላይ ልብ የሚያደማም ከሀዲነት ይስተዋላል:: የሀይማኖት እና የቋንቋ ልዮነት ሳይኖር በህብረት የጣሊያንን ወራሪ ጦር ለመመከት ለኢትዮጵያ የነበረውን ታማኝት( ከኤርትራውያኖች ጭምር -ገጽ 138 ላይ እንደተመለከተዉ) እና ቁርጠኝነት ያህል ክህደትን መርጠው ኢትዮጵያን የወጉም ነበሩ:: ክህደት የአማኝ ህዝብ መገለጫ አይደለም:: ከጣሊያን ጋር የሞተ የትግል ሽረት ትግራይ ላይ ሲደረግ ራሳቸውን እንደሺፍታ አደራጂተው በእምየ ኢትዮጵያ ልጆች ላይ አደጋ የጣሉትን የጣሊያን ቅጥረኞች እና ባንዶች እንርሳቸው እንኳን ቢባል አሁን ያሉት ህወሀቶች እና ደጋፊዎቻቸው የሚሄዱትን አኳሄድ እና ባህሪ ከገንዘብ ጋር ያላቸው ትስስር እና አሁንም ድረስ ያለው ዘረፋ እንዳንረሳ ያደርገናል::

የኢትዮጵያ ጦር በጣሊያን ሰራዊት ለመፈታቱ የሀበሻ ጀብዱ ጸሀፊን ጨምሮ ሌሎች በቦታው ያልነበሩ ሰዎችም የሰጡት አስተያየት አለ:: ጣሊያን የትጥቅ እና ሎጂስቲክ የበላይነት ነበረው:: የጣልያን አየር ሀይል የተጫወተው ሚና አለ:: የመገናኛ እና የመረጃ ችግርም እንደነበረ በዚሁ በሀበሻ ጀብዱ ንባቤ ተረድቻለሁ:: ንጉሰ ነገስቱ ለሰላም በነበራቸው ተስፋ ምክንያት በመከላከል ላይ የተመሰረተ ውጊያ እንዲካሄድ ከማዘዛቸው ጋር ተያይዞ የንጉሰ ነገስቱን ትዕዛዙን ለመቀበል ብቻ ሲባል (ጠንካራ የዕዝ ማዕከላዊነት) ጣሊያኖችን ላይ በከበባ አደጋ መጣል እና ማሸነፍ እየተቻለ ጣሊያን ጊዜ እንዲገዛ እና ራሱን እንዲያደራጂ የሆነበት ሁኔታም እንደነበረ ተረድቻለሁ:: እንደዛም ሆኖ ግን የኢትዮጵያ ሰራዊት በተንቤን የመጀመሪያውን ጦርነት ካሸነፈ በኍላ በሁለተኛው የተንቤን ጦርነት ተሸንፎ እንደገና ሀይሉን አስተባብሮ ማይጨው ላይ ጣሊያንን ሲገጥም ለማሸነፍ ተቃርቦ እንደነበር ጸሀፊው ይናገራሉ:: የትግራይ ሽፍቶች ናቸው የተባሉት ግን ተመሳስለው ገብተው ከኍላ የምየ ኢትዮጵያን ጦር በማጥቃት የኢትዮጵያ ጦር እንዲሸነፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል:: በዛ ላይ ተመሳስለው ገብተው ወሬ እየሰለሉ ለጣሊያን ሲያቀብሉ የነበሩትም እነሱው ናቸው:: ይሔ ደሞ ለጣሊያን ድል ጠቃሚ ሚና አልተጫወተም ማለት አይቻልም::

አሁንም የሀባሻ ጀብዱ ጸሀፊ አዶልፍ ፓርለሳክ እንደሚነግሩን( በቦታው የነበረ እንደመሆኑ የበለጠ የሱ ሊያሳምን ይችላል) ራስ ሙሊጌታ ልጃቸውን (ከፈረንሳይ ሀገር ትምህርቱን አቋርጦ ሊዋጋ የመጣ ልጃቸው ነው) አስከትለው በፈረስ ወደ አሸንጌ እየተሻገሩ እያሉ ተደብቀው ተኩሰው የገደሏቸው ራሳቸውን የትግራይ ሽፍቶች ነን የሚሉ ነበሩ:: የወደቁትን አባቱን ሊያነሳ ከፈረስ የወረደው ልጃቸውም እንዲሁ በነዚሁ “ሽፍታ ነን” በሚሉ ከሀዲዎች እና ከይሲ አልሞ ተኳሾች ነው የተገደለው:: እንደሚገባኝ እንደዚህ አይነቱ ነገር ያለመረጃ ልውውጥ እና ስለላ የተሰራ ላይሆን ይችላል:: አንድ የኢትዮጵያን የጦር መሪ ---ራስን ያህል ነገር ሲገደል ከጣሊያኖቹ የሚኖረውን ሽልማት ልብ ይሏል::

በዚህ ክህደት እና ዘረኝነት ግራ የተጋባው ጸሀፊው የጠየቀው ጥያቄ እና ያገኘው መልስ እንዲህ ይነበባል:-
ከመሀል ሀገር ስድስትና ሰባት ወር ሙሉ ፍዳውን እያየ ሲጓዝ ከርሞ እዚህ የደረሰው ወንድማቸው የነዚህን ሚስኪኖች [ዘራፊ ነን የሚሉትን እና የትግራይን ህዝብ] ህይወትና ንብረት ከጠላት (ለመከላከል የገዛ ህይወቱን አደጋ ላይ ጥሎ: ቤት ንብረቱን በትኖ መከራውን ባየ ለምን ይገድሉታል? ስል በድጋሚ አቶ ኪሩቤልን ጠየኩት …
‘አብዛኛዎቹ የትግራይ ሰዎች ይሄንን የተቀደሰ ሀሳብ ይቃወሙታል’ አለኝና ቀጥሎ ‘አንዳንዶቹ ይሄ ከመሀል ሀገር የመጣው የአማራና የኦሮሞ ሰራዊት በትግራይ ከከረመ ያለውን አዝመራ ከብትና ፍየል ይፈጀዋል በለው ይፈራሉ:: ሌሎች ደሞ ጣሊያኖች እስካሁን የወረሩት የትግራይን ግዛት ብቻ ነው እናም ትግራይን ከጠላት ለመከላከል ብቸኛ መብት ያለው የትግራይ ሰው ብቻ ነው ብለው ያምናሉ:: …
...ቀጥሎም ጣሊያኖች ይኼንን ችግር ጠንቅቀው ስለሚያውቁ በአማራው እና በኦሮሞው ጦር ላይ ትግሬዎች መሳሪያ እንዲያነሱ በሰላዮቻቸው አማካይነት ሲሰብኩና እና የነገር እሳት ስቆሰቁሱ እንደከረሙ ጨምሮ ነገረኝ:: ገጽ 121- 122

ሌላ ቦታ ላይ ደሞ እሱ (አዶልፍ ፓርለሳክ) በነበረበት ቦታ ያጋጠመውን እንዲህ ጽፏል :-
...እኛ [እሱ እና ሌላ አውሮጳዊ] እንዲህ በትዝታ ርቀን ከጦር ሰፈራችን ራቅ ብሎ አልፎ አልፎ ድው! ድው!ደው! የሚሉ የተኩስ ድምጾች እንሰማለን:: እዚህም የትግራይ ሽፍቶች ለዘረፋ ይመጣሉ:: ምን ያድርጉ! ጣሊያኖች በመሳሪያና በገንዘብ ይረዱአቸዋል:: ለዚህም ይመስለኛል በደጃዝማች አበራ ዋሻ ደጃፍ ሁለት አነስ አነስ ያሉ መትረየሶች የተጠመዱት::
የትግራይ ሺፍቶች ብዙ ጊዜ በድፍረት እስከ ጦር ሰፈራችን እምብርት ድረስ ዘልቀው ለመዝረፍ ሞክረዋል:: ሽፍቶችን ከሌላው የባላገር ወታደር መለየት አስቸጋሪ ነው:: ሽፍቶቹም ልክ እንደባላገሮቹ ወታደሮች ሁሉ የሚለብሱት ያደፈ ሸማ ነው:: እና በመጀመሪያ እይታ ማንም ሰው ሽፍቶች መሆናቸውን መገመትም መለየትም አይቻለውም:: ገጽ 149

እንዲህ ያለው ክህደት እና ዝርፊያ ነጻነት ሲመለስ ያስከተለው ነገር እንደሚኖር መገመት አይከብድም:: የአጼ ኃይለስላሴ መንግስት “ሆደ ሰፊነት” በሚል ፈሊጥ በባንዳዎቹ ላይ ሀጢያታቸው እንዲበዛ ባያደርጉም በባዶ እግሩ ትግራይ ድረስ በመከራ ሊዋጋ ሄዶ ክህደት የጠበቀው እና በከሀዲወች በመንፈስም በስጋም የደማው የባንዳ ወገን የነበረባቸውን ቢጎስም እና ብድር ቢመልስ በኍላ መልኩን ቀይሮ የብሄር ጭቆና ታርጋ ተለጥፎለት መጡ:: “የብሄር ጭቆናም” ተብሎ ከቀዳማዊ ወያኔ እንቅስቃሴ ወጣ የሚባለው የባንዳዎች የመንፈስ ልጂ ህወሀት ሊታገል ሲነሳ አሁንም “ትግራይን ነጻ በማውጣት” በሚል ፈሊጥ ነበር:: በትግራይ የነበሩ የአርበኛ ልጆችም የፕሮፓጋንዳውን ምንጭ እና ዘዴ ሳይገባቸው ከህወሀት ጋር አብረው እንዘጭ እንዘጭ ብለው አንዳንዶቹ በስተመጨረሻ ህይወታቸውን አጡ:: አንዳንዶቹ ተባረሩ::


አነሳሴ በመጻሀፉ ላይ ያስደመሙኝን አንዳንድ ነገሮች ማካፈል ቢሆንም እያነበብኩ እያለሁ በማገናዘብ ብቅ የሚል ስዕል የነበረኝን ጥርጣሬ እንድገፋበት አደረገኝ:: ህወሀቶች ከየት እንዴት እና ለምን እንደመጡ የሚጠቁም (እንደጠቆምኩትእንደዛ ተብሎ የተጻፈ የለም ---ስንተነትን ግን የምናገኘው ይሄንኑ ነው::) ሳልጠቅስ ማለፍ እንደሌለብኝ አመንኩ:: ከደርግ በኍላ የአርበኛ ልጆች በነበሩ ጭምር ተከልለው ወደ ስልጣን የመጡት የባንዳዎቹ ልጆች የነበረውን የኢትዮጵያዊነት ስሜት ከነደፉት ጎሳን ያማከለ የፖለቲካ አደረጃጀት ሌላ በ 'ህገ-መንግስት" እና በአዋጂም ጭምር ሊያጠፉት ሞከሩ:: እጂግ በጣም የሚገርመው ነገር በባዶ እግራቸው ለረሀብ እና ለሌሎች ችግሮች ሳይበገሩ ከዘመናዊ ጦር ጋር የተጋደሉትን እና ከሀገር በላይ የማይወዱትን ነብሳቸውን አሳልፈው የሰጡትን በመጥፎ ሁኔታ ስሎ የጀግንነት መጀመሪያ እና መጨረሻ ተምሳሌት የህወህት ታጋይ ይመስል ጧትና ማታ ስለ ህወሀት ጀግንነት በትግሪኛ እና በአማርኛ ተለፈፈ በቴሌዝዥን እና በራዲዮ እንድንሰማ ተደረገ:: በዚህ ሂደት ውስጥ እውነተኛዎቹን ለኢትዮጵያ የደሙትን የሞቱትን ጀግኖች በትግራይ መሬት ከጥሊያን ጋር ሲዋደቁ እዚያው በዱር በገደል የወደቁትን ጀግኖች እንዳይነሱ ተደረገ:: ተርጓሚው በእውነት ይሄንን ስራ ለዚህ ትውልድ በማበርከቱ ትልቅ ስራ ሰርቷል:: በህወህት ዘመን ተወልደው ህወሀት ""ጀግና ነኝ:: ጀግና ተፈጥሮ አያውቅም እያለ"" ሲለፋደድ እየሰሙ ያደጉት እና ዛሬ በወጣትነት እድሜ ላይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንዲህ ያለውን ስራ እንዲያነቡ መምከር ያስፈልጋል ባይ ነኝ:: አምላክ ብርታትን ሀይልን ይስጠን::


Friday, April 20, 2012

""ሁሉ አይጠየቅም::" "ሁሉ አይነገርም::"...?



""ሁሉ አይጠየቅም::"" ""ሁሉ አይነገርም::"" የሚለውን እሳቤ ወደ ልቤ ልወስደው እልና ታዲያ እንዴት መማማር ወይ መግባባት ይቻላል የሚል ነገር ይመጣብኛል:: ያለ ንግግር በምልክክት መግባባት ቢቻል አንዳንዴ ንግግርን ማስቀረት እርግጥ ይጠቅም ይሆናል:: አይቻልም::

ሰው የሚናገረው ወይ የሚጠይቀው ነገሮችን ለመለወጥ ወይንም መልስ አገኛለሁ ብሎ አምኖም ላይሆን ይቻላል::ጥያቄው እንደጥያቄ መሰንዘሩ ወይ ደሞ መነገር የለበትም ተብሎ የሚታሰበው ነገር በመነገሩ ከእፎይታ ስሜት ባለፈ ; ነገሮችን ለሰው ከማካፈል ስሜት ባለፈ ; ጥያቄየን ወይንም ሀሳቤን በግላጭ ማውጣቴ ቢያንስ ባጋጣሚ ካለማወቅ እና ከግንዛቤ እጥረት የመጣ እንኳን ቢሆን የመማር ዕድሉ ይኖረኛል ብሎ ከማሰብም የመነጨ ነው::

ሰላማዊ ሰልፍ የሚባል ነገር ከወጣሁ ሰንብቻለሁ:: ጊዜ አጥሮኝ ወይ መገኘት ሳልችል ያልተገኘሁባቸው ግን ጥቂቶች ናቸው:: ብዙ ጊዜ የማልሄድበት ዋነኛ ምክንያት የሚያስቆጣን በሀገር ላይ የሚቃጣ የህወሀት ጥቃት እዚህ ውጪ ሀገር በሚደረግ በፔቲሺን እና በሰላማዊ ሰልፍ ይቀየራል ብየ ስለማላምን ነው:: ምንም ያህል እውነት ብንይዝም ምንም አይነት የፍትህ ጥያቄ ብናነሳም በዓለማችን ባለው ነባራዊ ሁኔታ እንደምናየው የዐለም ዓቀፍ ፖለቲካ በመርህ እና በፍትህ የተመሰረቱ ናቸው ብየ ስለማላምን ነው:: በታሪክም ይኸው ነበር ሁኔታው:: አሁን ባለንበት ዘመን ደሞ ችግሩ እየከፋ መጥቷል:: አንዳንዴ እንደ ህወሀት ያለ ቡድን በቀዳሚነት ቅጥ ያጣ ዓለም አቀፍ ርዳታ ተጠቃሚ የሚሆነበትን አገባብ አስቤ አስቤ በመርህ እና በፍትሀዊነት ላይ ያልተመሰረተ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ነጸብራቅ ( ወይ አንድ ማሳያ) ከመሆኑ በስተቀር ሌላ ምክንያት አጣለሁ::

ሀገሩን ተቀምቶ እየተዘረፈ በዚያም ላይ በርግጫ እን በጡጫ እየተረገጠ በአፈና ስር ያለው ኢትዮጵያዊን በጥርጣሬ እያዮ ረጋጩን ህወሀትን አንዳንዴ የሚቆጡ እየመሰሉ ርባና በሌለው መግለጫ ሌላ ጊዜ በዝምታ የሚደገፈው ህወሀት ነው:: ምንም እንኳን ተጨባጭ የሆነ ማስረጃ መደርደር ባልችልም ከማየው ነገር ግን የአለም አቀፉ ማህበረሰብ እና ሀያላን መንግስታቶች ምንም ቢያጠፋ ምንም የህወሀት ነገር አይሆንላቸውም የሚል እሳቤ ላይ እደርሳለሁ:: ከህወሀት የህዝብ ፍቅር አለመኖር እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታዛዢነት ጋር ሊያያዝ ይችል ይሆናል ጉዳዮ:: ቁም ነገሩ ግን ህወሀት በኢትዮጵያ ላይ እያደረሰ ያለውን ነገር ሀያላኑ መንግስታትም ሆኑ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሳምረው ያውቁታል:: የየቀኑ የየዕለቱ ዘገባ አላቸው:: በየአታሸዎቻቸው አማካይነት:: እኛ ታዲያ የሞኝ ፈሊጥ አይሉት ምን አይሉት ልክ እንደማያዉቁ ህወሀት ባወጣው እቅድ ቅደም ተከተል መሰረት አንድ ባንድ ጥፋት ሲያደርስ ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ እናሳውቃለን እያልን በየከተሞቹ ሰልፍ እንወጣለን:: ልክ እንደማያውቁ:: አልዋጥልህ እያለ ከሰልፍ ያስቀረኝ የነበረው ጉዳይ::

ዛሬ ግን ለራሴ የገባሁትን ቃል-ኪዳን አፍርሼ እንደገና ለሰልፍ ወጣሁ:: የሰልፉ ጉዳይ የዋልድባ ነገር መሆኑ እና ቢያንስ በዚህ ጉዳይ ክርስቲያኑ ህዝብ እየተሰለፈ ከሰልፉ ቦታ መሰወር ( በስራ ምክንያትም ቢሆን) እንደሌለብኝ ባምንም ሰልፉ የተደረገው በኦንቴሪዮ መንግስት (የአውራጃ አስተዳደር እንበለው) ፓርላማ እንደመሆኑ የዋልድባ ጉዳይ በእርግጥም የኦንቴሪዎ መንግስት ጉዳይ ይሆናል ለዋልድባ ኬር ያደርጋል ከሚል እምነት አልነበረም:: ይሄ መንግስት ለጩኽታችን እጂግ በጣም ትኩረት ከሰጠ ሊያደርግ የሚችለው ጉዳዮ ለሚመለከተው ዩኔስኮ በካናዳ መንግስት አማካኝነት ለህወሀት መንግስት የተማጽኖ ደብዳቤ ይጽፍ ይሆናል --- እንግዲህ "what is there in it for us?" የሚለውን ከመለሱ ማለት ነው:: በሌላ አነጋገር ፊት ለፊታቸው ስለ ዋልድባ ገዳም የሚጮሑ ኢትዮጵያውያንን ገዳም እንዳይታረስ እና የስኳር እርሻ እንዳይሆን የሚታገሉበት ራሺናሊቲ የህወሀት መንግስት በኢንቨስትመት እና ባህል አንፅር ከሚሰጣቸው ጥቅም ራሺናሊቲ ከበለጠ ነው:: ለማንኛውም ባላምንበትም (በሰላማዊ ሰልፍ) መሄድ አለብኝ ብየ ራሴን ሳላሳምነው አዘዝኩት:: ሄጄም ግን አላፈርኩም ጥሩ ስሜት ተሰምቶኝ መጣሁ:: በተለየ ምክንያት ቢሆንም::

ከምንም ነገር በላይ ያስደሰተኝ የተደረገው ጸሎት ነው:: የኦንቴሪዮ ፓርላማ ፊት ለፊት ሆነን "" ስማነ አምላክነ ወመድሀኒነ"" ስንል ተስፋ ባላደርኩብት እና በማላደርግበት ተቋም ፊት ቆሜ የበለጠ መፍትሄ የሚሆን ሀያል አምላክን በዛች ቅጽበት በዛች ቦታ በማስታወሴ ተደሰትኩ::ከምርም ጸሎት አደረኩኝ:: ጸሎቴ ደሞ አግዚያብሄር ሀገር ቤት ላሉ ልባም እና ደፋር ልጆች የበለጠ ድፍረትን እና ማስተዋልን እንዲሰጣቸው እና ቁጥራቸውን ከእለት ወደ እለት እንዲያበዛው ነው:: የሚያባንኑ የሚቀሰቅሱ እና የሚመሩ ኢትዮጵያውያኖች እዚያው ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲፈጠሩ አያሰብኩ ነበር ""ስማነ አምላክነ ወመድሀኒነ"" ያልኩት::


ሁለተኛ ያስደሰተኝ ነገር የኢትዮጵያውያንን ሙስሊሞች ጨዋነት ዛሬም በማየቴ ነው:: ሀጂ መሀመድ የሚባሉ ኢትዮጵያዊ ከእኛ ከክርስቲያኖቹ እኩል ስለ ዋልድባ ሊጮሁ እና ወጣቱ ከተጠመደለት የሀይማኖት እና የዘር መከፋፈል እንዴት ስብሮ መውጣት እንዳለበት ሊያስታውሱ ነበር:: በሰል ያለ መልዕክት አስተላልፈዋል:: ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋት ወጣቶችም እንዲህ ያሉ ናቸው:: እውቅና እና መቻቻልን የሰነቁ:: ራዕይ ያላቸው:: የሀገራቸውን ጥቅም በምንም አይነት ሁኔታ አሳልፈው የማይሰጡ:: እነኚህ ነገሮች ጸሎት ብቻ ሳይሆን ማህበራዊ ዘመቻም እንደሚያስፈልጋቸው አምናለሁ:: በርዕዮተ ዓለም እና በፖለቲካ እይታ የሚደረገው ውይይት እና ክርክር በይደር ትቶ መጀመሪያ ማህበራዊ ንቃተ ህሊናን ወደ መቀስቀሱ ዘመቻ መገባት አለበት ባይ ነኝ::








Sunday, April 15, 2012

"ውሾን ያነሳ ውሾ ይሁን "?

ምንም እንኳን በአካል ሀገራችን ባንሆንም በመንፈስ እዛው ነን:: በተለይ እንዲህ ባለ የአውደ ዓመት ጊዜ:: በመገናኛ ዘዴው መርቀቅ እና ፍጥነት ምክንያት የመረጃ ልውውጡ የዛኑ ያህል ስላደገ እና የየደቂቃውን ጭምር መረጃ ማግኘት ስለሚቻል አሁን አሁን ሀገራችን ያለነው በመንፈስ ብቻ አይደለም ለማለት ያስደፍራል:: እዛው ያለሁ ያህል የማውቃቸው ጉዳዮች አሉ:: በዓይኔ በብረቱ ካላየሁ የሚባል ነገር ብዙም ትርጉም አይሰጥም በዚህ ዘመን:: እንዳይኔ ወይንም ከዚያ በላይ ሆነው ነገሮችን በሚዛናዊነት በመመዘን ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በትክክል የሚያቀብሉ ወገኖች ሳላሉን::

ትንሳኤ እንደመሆኑ እንደደንቡ ቤት ውስጥ እንዲኖር የሚያስፈልገውን የአውደ ዓመት መሰናዶ አድርጌ በላሁ ጠጣሁ ( እየጠጣሁም ነው በስሱ):: እየተሰማኝ ያለው መሳቀቅ (ብቸኝነቱን ለምጀዋለሁ) ግን እንዲህ እንዳይመስላችሁ:: ብዙ ወገኖቻችን በምን አይነት ሁኔታ እንደሚያሳልፉት እያስታወስኩ ነው:: የዶሮ እና የበግ ዋጋ ውሾን ያነሳ ውሾ ይሁን ተብሎ የሚተው ነገር ሳይሆን የኢኮኖሚ የባህል እና ማህበራዊ አንደምታው መመርመር ያለበት ነገር ነው::

ከቁም ነገር አዘል ቀልድ ጀምሮ እስከ ጠንከር ያሉ ዘገባዎች እና አስተያየቶች ተሰንዝረዋል:: ""እንደ እየሩሳሌም እንዳክሱም ጺዎን ተሳልሜው መጣሁ ዶሮና በጉን"" የሚል መልዕክት አንብቤ ከቀልድነቱ ይልቅ ሮሮነቱ ስላየለብኝ ምን መዐት መቶ ነው ዋጋ እንደዚህ ሰማይ የነካው ከሚል ሀሳብ ጋር ብዙ ቆየሁ:: በኔ እንኳን እድሜ ዶ/ሮ ከ5-10 ብር ባለው ሬንጂ ሲሸጥ አስታውሳለሁ:: ትልቅ የሚባል በግ በ75 እና 80 ሲገዛ አስታውሳለሁ:: እውነት ነው የብሩ የመግዛት አቅም እንደተዳከመ ይታወቃል:: በሁለት አስርት አመታት ውስጥ ግን ከመቶ ፐርሰትን በላይ የብር የመግዛት አቅም ሲወድቅ ምን እንደሚባል አላውቅም:: የሚገርመውን የአብዛኛው ሰው ገቢ ትርጉም ባለው ሁኔታ አለመጨመሩ ነው::

እየሆነ ያለው ነገር በቅንጂት እየተሰራ ያለ ነገር እንደሆነ መገመት ይቻላል:: የማን የማን እጂ እንዳለበትም መገመት ይቻላል:: በበዓል ቀን በግና ዶሮ ገዝቶ ከዘመድ ወዳጂ ጋር መቋደስ ለእርድ እና ለስጋ ያለን ፍቅር ሳይሆን የሚያመለክተው ማህበራዊ ፋይዳውን እና ባህላዊ ፋይዳውን ነው:: ብዙ ኢትዮጵያውያን እጂግ በጣም ደሀ እየሆኑ በሄዱበት ሁኔታ ትርጉም እና ክብር በሚሰጣቸው በዐል የሚገለገሉበት ሸቀጥ ላይ ቅጥ ባጣ ሁኔታ ዋጋ መቆለል በአነስተኛ ገቢ ባላቸው ወገኖቻችን ላይ ሳይሆን በባላችንና በማህበራዊ ግንኙነታችንም ላይ እንደተሰነዘረ ጥቃት መቆጠር አለበት:: ጥቃቱ የሚሰነዘርብን ለመጠቃት የተመቸን ስለሆንን እና ለለውጥ ስላልተነሳሳን ነው:: እንደ ህዝብ ስለማንፈራ እና ምን ያመጣሉ ስለምንባል ነው:: እንዲህ ባለ ሁኔታ መፍትሄው ዶ/ር ኃይሉ አርዐያ በመጨረሻው የፍኖተ ነጻነት እትም በሰጡት አስተያየት እንደሚሉት ""ያስጠቃን ባህላችን ነው:: የባህል ባሪያ ስለሆንን ነው:: ዶ/ሮ በ200 ብር ገዝቼ አላድርም ባህሌ ይቅር"" ሳይሆን የተቀናጀ በማይመስል ምናልባት ግን በደንብ በተጠና እና በተቀናጀ ሁኔታ በባህላችን ላይ ጥቃት እየሰነዘሩ ያሉ ሀይሎችን ለይቶ መታግል ያስፈልጋል::

Monday, June 27, 2011

በማንነታችን ላይ የተጋረጠ ፈተና

ትንሽ ቀደም ባለው ዘመን የመንግስትን ተፈጥሮ አና አስፈላጊነት ለማስረዳት ጠለቅ ያለ እሳቤ ያደረጉ የምዕራቡ ዓለም የፖለቲካ አሳቢዎች (Political thinkers) የመንግስትን አደረጃጀት እና በህብረተሰብ ውስጥ የሚጫወተውን ሚና ለመተንተን ከሰው ልጂ ተፈጥሮ ነው የጀመሩት:: የሰውን ልጂ ተፈጥሮ ብቻ ሳይሆን የሰው ልጂ በህይወት ዘመኑ የህይወት ግብ ሊሆን ስለሚገባው ነገርም ሀሳብ ሰጥተዋል:: እነዚህ አሳቢዎች በሰው ልጂ ተፈጥሮ ላይ የበነራቸው አመለካከት እንደሚለያየው ሁሉ የሰው ልጂ በህይወት ዘመኑ እንደ ግብ እና የህይወት መርህ ሊይዘው ይገባል በሚሉትም ነገር ላይ ልዮነት አላቸው:: እንዳንዶች ( እንደ ጆን ሎክ ያሉ) መኖርን ወይ አድሮ መገኘትን (preservation of life ብለው የገለጹትን ) እና ቁሳዊ ብልጽግና የሰው ልጂ ዋነኛ የህይወት ግብ ነው የሚል ሀሳብ ሲያራምዱ ሌሎች ደሞ ሰውን ሰው የሚያደርገው እንደ እንስሳ አድሮ መገኘት እና የእንስሳዊ ህይወት መኖር ሳይሆን ስው ለክብሩ መኖር እና ለዛም እውቅና (recognition) ለማግኘት ህይወቱን እስከሚያጣም ድረስ ቢሆን ሲታገልለት ነው የሚሉ ነበሩ (ሄግል በዋነኛነት ይጠቀሳል):: በኍለኛው አስተሳሰብ መሰረት ምንም ያስከትል ምን (-ሞትን ጨምሮ ) የሰው ልጂ ትግል መሆን ያለበት ስብዕና እና ክብር ላለው ይህወት ነው:: እንደ እንስሳ መኖር እና ቁሳዊ ሀብት ማፍራት ትርጉም የለውም :: የሰው ልጂ ስብዕናው እና ክብሩ እውቅና ባልተሰጣቸው ሁኔታ ትግሉን ማቆም የለበትም የሚል አስተሳሰብ ላይ ያተኩራል::

ቁሳዊ ሀብት ብቻ ማከማቸት የህይወት ትርጉም እና ግንዛቤ መነሻ እና መድረሻ ባልነበረበት - የካፒታሊዝም ስርዐት የምርት ሂደቱን በማስፋፋት የሚመረተው ምርት በሙሉ ተጠቃሚ እንዲያገኝ የተጠቃሚ ማህበረሰብ የመፍጠሪያ ዘዴ ሳይስፋፋ እና ሰዎች የማያስፈልጋቸውን ነገር ልክ እንደሚያስፈልጋቸው እንዲያምኑ እና እንዲገዙ ከመደረጉ በፊት- ከመሬት ሌላ ለሌሎች ሀብቶች ብዙም በማይማለልበት ፊዎዳላዊ በሆነ ማህበረሰብ ውስጥ ክብር ትልቅ ቦታ ነበረው:: ""ክብር"" በቁሳዊነት ላይ የሚያተኩረውን ሀሳብ ለሚያራምዱት የማይጨበጥ የማይዳሰስ የማይኖር - አዲያሊስት ነው ይሉታል:: የጀነት ወይንም የመንግስተ ሰማያት ሀሳብ ሰዎች የሚኖሩለት በአይን ስለሚታይ ወይንም በእጂ ስለሚዳሰስ አይድለም:: በተመስጦ ; በእሳቤ እና በእምነት ስለሚታይ ነው:: ነብዮ መሀመድ የደረሰባቸው ነገር የደረሰባቸው ለእምነት ነው:: የክርስቶስ ተከታዮች የሞቱት ለእምነት ነው:: በሩቅ ምስራቅ የተነሱ ሌሎች የእምነት መምህራን የደረሰባቸው እንግልት የደረሰባቸው ለእምነት ነው:: ቅጥ ያጣ የማቴሪያል ፍላጎትን መቆጣጠር እና ለክብር ቦታ መስጠት በተወሰነ መልኩ መንፈሳዊ ገጸታ አለው ብየ አስባለሁ:: እንደገባኝ በየትኛውም እምነት ከልክ ያለፈ ስግብግብነት እና ማቴሪያል የማከማቸት ፍላጎት አይበረታታም:: ክብርን እና የሰውነት ትርጉምን በማጣት የሚገኝ ሀብትም ሆነ መሰንበት የሰውን ልጂ ደስተኛ አለማድረጉ ብቻ ሳይሆን :: ለማቴሪያል የሚኖር ማህበረሰብ ግለኛ እና የተበታተነ ነው:: ለሀሳብ እና ለእምነት ( ማህበራዊ; ባህላዊ; ሀይማኖታዊ ) የሚኖር ማህበረሰብ ደሞ ማህበራዊ አስተሳሰብ ያለው ለወንጀል ሆነ ለስግብግብነት ሆነ ሀገር ለመክዳት ሆነ እና ለሌሎች መጥፎ አንድምታ ላላቸው ማህበራዊ ደዌዎች መሰረት ሊሆን አይችልም:: በእንደዚህ አይነት ማህበረሰብ ውስጥ የጋራ የሆነ የሚከበር ማህበረሰባዊ ህግ ስለሚኖር ነውር ;ወንጀል እና መሰል ነገሮች ቦታ አይኖራቸውም:: ሀገራችን ኢትዮጵያ እንደዚህ አይነት ማህበረሰብ ከታደሉት ውስጥ አንዷ ነበረች:: እነዚህ ነገሮች ከማህበራዊ ህግጋትም አልፈው ባህልም ሆነው ነበር:: በቅርቡ የምንሰማቸው የተማሪዎች ሴተኛ አዳሪ መሆን ; የወንጀል መበራከት ; ስግብግብነት በወንጀል እና ዘረፋ ለሚያምን የፖለቲካ ቡድን ተባባሪት የሚያመላክቱት ነገር ቢኖር ከማህበራዊ ማንነታች ምን ያህል እያፈነገጥን እንደሆነ ነው:: በእንደዚህ አይነት ሁኔታም ጸሀፍቶች የሚተቹን የኢትዮጵያን ባህል ነው::
አሁን አሁን የተነሱ ጸሀፍት ብዕራቸው የኢትዮጵያን ባህል እና ታሪክ ለመተቸት የሚነቃውን ያህል ኢትዮጵያን በነጻነት ጠብቆ ለማቆየት የተደረገውን ትግል እና ማህበራዊ እሴቶቻችንን ( ለምሳሌ እንደ ይሉኝታ እንደ ክብር እንደ ነግበኔ የሀገር ፍቅር ያሉ ነገሮችን) እና የህይወትን እይታ ጭምር በስከነ መንፈስሊመረምሩ ሲፈልጉ አይስተዋሉም:: በሌላ አነጋገር በኢትዮጵያዊ በባህል ላይ አመጽ ለማቀጣጠል የሚፈልጉ ኢትዮጵያ ሶስት ሺ ዘመን ተኝታለች ብለው የሚያስቡ አይጠፉም:: እርግጥ ነው ባህል እና እና ማንነት ማህበራዊ ስሪት (social construction) ነው:: የኢትይጵያን ማህበረሰብ በታሪክ በኢትዮጵያ ውስጥ የነበረውን ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ መስተጋብር ሆነ ; ማህበራዊ ስሪት የፈጠረውን ኢትዮጵያዊ ባህል እና ኢትዮጵያዊ ማንነት ከውጭ ሀይሎች ጥቃት ጠብቆ ለማቆየት የተደረገውን ትግል ስናይ- በኢትዮጵያ ማህበረሰብ ውስጥ ""የህይወት ትርጉሙ ነብስን ማቆየት እና ሀበት ማፍራት እንደ እንስሳ መኖር"" የሚለው አስተሳሰብ ቦታ እንዳልነበረው እንረዳለን:: ይልቁንም በኢትዮጵያ ትልቅ ቦታ የነበረው አይዲያሊስት እይተባለ የሚጣጣል ነገር ግን በህይወት ውስጥ ትልቅ ፋይዳ ያለው ""ሰው ያለ ክብሩ ምንድን ነው?”"" የሚል አስተሳሰብ ነበር:: የኢትዮጵያ ክብር ነጻነት እና አንድነት ተጠብቆ ሊቆይ የቻለው ለክብር ; ለነጻነት እና ለአንድነት ክፍተኛ ቦታ የሚሰጥ ወደ ባህል የተቀየረ ማህበረሰባዊ አስተሳሰብ ስለ ነበረ ነው:: የሰው ልጂ ስብዕና እና ማንነት መመዘን ያለበት ለክብር በሚሰጠው ቦታ እንጂ ለስግብግብነት እና ስግብግብነት ለሚወልደው በወንጀል ላይ ለተመሰረተ ክብረት አን ሀብት መሆን የለበትም:: አልነበረምም በታሪካችን:: ከዚህ ጋር ተያዮዞ ነው - ነውር; ይሉኝታ ነግበኔ እና ሌሎችም ማህበራዊ ዕሴቶቻችን የማህበራዊ ህግጋታችን መስፈሪያዎች የነበሩት:: የክብር እና የመከበር ነገር የሚገባው ዜጋ ለነውር እና ለይሉኝታ ይገዛል:: ምክንያቱም ነውርን እና ይሉኝታን ሲረሳ የሚጎዳው ክብሩን ስለሆነ:: በጋራ የተፈጠረውን ማህበራዊ ህግ ( ይሉኝታን እና ነውርን ጨምሮ) የሚያከብር ራሱን ያከብራል:: ለክብር የመሞት ነገር መሰረቱ የተተከለው በዚህ መልክ ነው:: የጀግንነት መሰረቱ የሚወሰነው ለክብር በሚሰጠው አመለካከት ነው:: በፆታ ግንኙነት እንኳን አፍቃሪ የእጮኛውን ልብ የሚገዛው በክብሩ ላይ የማይደራደር ሲሆን ነው:: ይቀነቀን የነበረ '' ወይ ግደልላት ወይ ሙትላት የፈሪ ወዳጂ አታስብላት"" ለጀግንነት እና ለክብር የሚሰጥ ዋጋ ነጸብራቅ ነው::

ይሄ ማህበረሰባዊ ክብር እና ማህበራዊ ህግ የሀገርም መለያ ነበር:: በኢትዮጵያ ላይ የሚሰነዘር ጥቃት በያንዳንዱን ኢትዮጵያዊ ላይ እንደሚሰነዘር ጥቃት ነው የሚለውን እምነት ኢትዮጵያውያን በተግባር ኖረውታል:: እንደዛ ባለው ዘመን ኢትዮጵያ ወረራ በተቃጣባት ቁጥር ኢትዮጵያውያን ለመግደል ወይ ለመሞት ነው የሚያኮበኩቡት:: ከእንደዚህ አይነቱ ተጋድሎ ራሱን የሚያገል ማህበራዊ ተቀባይነት አልነበረውም:: በዚያን ዘመን እናቶች ልጆቻቸው የሀገርን ክብር ለማስተበቅ ለዘመቻ ሲነሱ እንደኛ ዘመን እናቶች አትሂድብኝ ትሞትብኛለህ አይሉም:: ይልቁንም ስንቅ አደራጂተው በደስታ ይቅናህ ቀኙን ይስጥህ ብለው መርቀው ይሸኛሉ:: የበረቱትም ይከተላሉ:: የኢትዮጵያን የታሪክ ማህደር ስናገላብጥ ትልቅ ታሪክ ያስመዘገቡት አንድ ለናቱዎች ሆነው የምናገኝበትም ሁኔታ አለ:: ሚስቶችም በእንደዚህ አይነት ጊዜ ባሎቻቸውን አበረታተው ይሸኛሉ:: ይከተሉማል:: ይሄ እንግዲህ አንድም ከኢትዮጵያ ጋር የነበረው ትስስር እና ኢትዮጵያ በኢትዮጵያውያን የነበራት ቦታ የተከበረ እና የተወደደ በመሆኑ ነው:: አንድም ኢትዮጵያውያን ለህይወት እና ለክብር ይሰጡት የነበረው ትርጉም ጥልቅ ስለነበረ ነው:: አፄ ቴዎድሮስ የራሳቸውን ህይወት የወደሱብት እምነት አስብ እንደነበረው ምን አይነት ወንድ ነው ክንዴን ሳልንተራስ ክንዴን የሚጨብጠው ከሚል ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ንጉስ አይማረክም ከሚል ለኢትዮጵያም ከነበረ ጥልቅ አክብሮት እና ፍቅርም እንደነበር አንድ ጓደኛየ በቅርቡ አጫውቶኛል:: ይሔም ለነፃነት እና ለሀገር የነበረ አስተያየት ቀናኢነት ብቻ ሳይሆን ለህይወትም ይሰጥ የነበረውን ፋይዳ እና ትርጉም ያመላክታል::የአልሸነፍ ባይነቱ ሚስጥር በህይወት ትርጉም ላይ ከነበረ ጥልቅ እይታ እና ጥርት ያለ አቋም የመነጨ ነበር:: ኢትዮጵያ (ከፈጣሪ ጥበቃ መልስ) ነጻነቷ ተከብሮ የቆየበት ሚስጥር ይሄው ነው:: የኢትዮጵያውያንም ምኞት እና መፈክር ""ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!"" የሆነበትም ምክንያት ይሄው ነው::

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ እየተተከሉ እና ተቀባይነት እያገኙ የመጡአዳዲስ ማህበራዊ አስተሳሰቦችን እና ልማዶችን ግምት ውስጥ በማስገባት እውነት ""ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኖራለች ወይ?"" ወይንም ""ለዘላለም የምትኖርበት ሁኔታ አለ ወይ?"" ብለን ስንጠይቅ ትንሽ ስጋት የሚጋርጡብን ሁኔታዎች ያሉ ይመስለኛል:: አለን እንል የነበረው ነገር ባህል እና ማህበራዊ እሴት ነበር:: ነውር; ይሉንታ ; የሀገር ፍቅር እና በሀገር ላይ ልክ ያልሆነ ነገር ሲደረግ የመጠቃት; የመቆጨት እና የመቆጣት ስሜት ነበር:: በታሪክ ኢትዮጵያውያኖች በጭፍን ነገስታቶቻቸውን የሚከተሉ አልነበሩም:: ንጉስ ተቀባይነት(legitmacy) የሚያገኝባቸው መሰረታዊ ነገሮች አሉ:: ለምሳሌ በመካከለኛው ዘመን አውሮፓውያን የጎንደር ነገስታቶችን አማለው እነሱን ካቶሊካዊ ካደረጉ መላውን ኢትዮጵያን በቀላሉ ካቶሊካዊ ማድረግ እንደሚቻል ያምኑ ነበር:: ያሰቡትንም ሞከሩት:: የተወሰኑ የጎንደርን ነገርታቶች ቀየሩ:: ነገስታቱም የተቀበሉትን አዲስ እምነት በኢትዮጵያውያን ላይ ለመጣል አዲስ አካሄድ ጀመሩ:: የተከተለው ነገር ግን ቁጣ እምቢተኝነት እና ጦርነት ነበር:: ነገስታቱም ተሳስተው እንደነበር አምነው ሕዝብ አሸነፈ::

ከላይ እንደጠቀስኩት ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ የሚያሰኛት ወይንም ኢትዮጵያን ከሌላው ማህበረሰብ የሚለያት መልከዐምድራዊ አቀማመጧ; እና በኢትዮጵያ ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች ብቻ አይድሉም:: ማህበራዊ ስሪቱ እና በዘመናትየተገነባው ባህላዊ እኛነታችን ነው ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ የሚያህብላት::ኢትዮጵያ ቀጥላለች የሚባለው ይህ በዘመናት የተገነባ እና ብዙ ኢትዮጵያውያን በህይወት የከፈሉበት እሴት ቀጥሎ ከሆነ ነው:: ለምሳሌ ለኢትዮጵያ ያለ ፍቅር እና ከኢትዮጵያ ጋር ያለ ትስስር; ማህበራዊ ህግጋቶቻችን ( ነውር; ነግበኔ ) እና ሌሎችም:: ክብሩን እና የሀገር ፍቅሩን በመኖር የማይቀየርባት በነበረች ኢትዮጵያ ማን ኢትዮጵያዊ ወጣት በስራ ዕድል እና ሌሎች መደለያዎች መሰሪ ለሆኑ ሀይሎች ጋሻ አጃግሬ ይሆናል ብሎ ያስብ ነበር? ነውር እና ክብር የማህበራዊ ተቀባይነት መሰረት በነበረባት ኢትዮጵያ ማን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሴተኛ አዳሪነት ይሰማርሉ ብሎ ያሰበ ነበር?? ማን በኢትዮጵያ ውስጥ ሴቶችን እርቃናቸውን እና ሀፍረታቸውን በእግዚቢሽን መልክ እያሳዮ ገንዘብ የሚቀበሉበት ዘመን ይመጣል ብሎ የገመተ አለ? ማን ግብርና እና ገበሬነት ላብዛኛው ህዝብ መተዳደሪያ በሆነባት ኢትዮጵያ አንድ አገር የሚያክል የኢትዮጵያ መሬት ለውጭ ቱጃሮች ሲቸበቸብ ያለ ቁጣ እና የለ ንዴት በዝምታ እና በግዴለሽነት የሚያይ ትውልድ ኢትዮጵያ ውስጥ ይፈጠራል ብሎ የሚያስብ ነበር?? (አሁን “”ያልታረሰ እና አይን አይኑን ሲታይ የነበረ መሬት ነው”” እየተባለ ለውጭ ኢንቬስተር እየተሰጠ ያለው መሬት የኢትዮጵያ ነገስታቶች በቅኝ ግዛት ይዘው በዝብዘውታል ሲባል የነበረ የኢትዮጵያ ክፍል ነው:: )ማን ኢትዮጵያውን ነብሳቸውን እስከሚስቱ ድረስ ከሚወዱአት አገራቸው ጋር ያላቸው ትስስር የላላ እና የይስሙላ ይሆናል ብሎ የገመተ ነበረ?? በጥቂት አስርት አመታት ውስጥ የተከሰተው ይሄ ሁሉ ውጥንቅስ የምን ውጤት ነው?? ማህበራዊ ህጋችንን የሰባበረው ማን ነው?? በምን አይነት ዘዴ?
ምንም እንኳን ከውጭም ከውስጥም በረቀቀም ባልረቀቀም መንገድ ኢትዮጵያውያ አሁን እየሄደችበት ወዳለው ማህበራዊ ቀውስ እና ማንነት የማጣት መስመር ለመውሰድ የተጉ እና አሁንም የሚተጉ ሀይሎች ቢኖሩም : የሆነው ነገር ሁሉ ግን የሆነው ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር ብለን የምናስብ ወገኖች አደጋውን በጥሞና ተረድቶ ኢትዮጵያን ለዘላለም ለማኖር የሚያስቺል ስልታዊ እና የተቀናጀ አካሄድ ለመሄድ ባለመቻላችንም ነው:: የኢትዮጵያ ጠላቶች ብርታት ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያውያንም ድክመት ነው የችግሩ ምንጭ:: የኢትዮጵያን ለዘላለም መኖር ለማረጋገጥ የፖለቲካ እንቅስቃሴ እያደሩረጉ ያሉትም ያንን ዐላማ በማሳካት ረገድ ባህል የሚፈጥረውን ጉልበት እና አቅም የተረዱት አይመስሉም:: እንደውም ለተጨቋኝነታችን ምክንያቱ ባህል ነው ብለው የሚያስቡም አይጠፉም:: የኢትዮጵያ ባልህ ባይተዋር ሆኖ እንደባላንጣ የሚታይበት እና ላለመሰልጠናችን እንደምክንያት የሚቆጠርበትም ጊዜ አለ::

አንግዲያውስ ኢትዮጵያ ለመታደግ ትርጉም ያለው ስር እንስራ ካልን የባህልን ግብዕትነት ተጠቅመን ወጣቱ ከማንነቱ እና ከባህሉ ጋር በአክበሮት እና በፍቅር የሚኖርበትን ሁኔታ መፍጠር ያስፈልጋል:: ይሔንን ለማድረግ ብዙ አማራጮች አሉ:: አሁን ኢትዮጵያን እየመራ ያለው ቡድን ድንጉጥ ባህሪ ስላለው እሱን በማያስደነግጥ እና ሌላ እርምጃ ለመውሰድ በማያነሳሳው መልኩ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በመላው ኢትዮጵያ በባህላቸው እና በሀገራቸው ላይ የሚወያዮበትን እና የሚመክሩበትን የራሳቸውን መድረክ እንዲፈጥሩ እገዛ በማድረግ መጀመር ይቻላል:: ኢትይጵያን ለማዳን መጀመሪያ ማህበራዊ ቤዝ መፍጠር ያስፈልጋል:: ይሔንን ለማድረግ ደሞ የማህበራዊ ቆሻሻውን የሚያጽዱ እና የሚያጸዱ ሌሎች ጋሽ አበራ ሞላዎች ያስፈልጋሉ:: በዲያስፖራ የምንገኝም ይሄንን በማገዝ ረገድ ትልቅ ሚና መጫወት እንችላለን ማድረግም አለብን:: የኢትዮጵያ ምሁራኖችም ኢንተሌክቹዋል እንቅስቃሴ መጀመር ያለባቸው ይመስለኛል:: በኢትዮጵያዊ እሴቶቻችን ላይ በሰከነ መልኩ ሪፍሌክት ማድረግ አልጀመርንም ባይ ነኝ:: ቻይናዎቹ የአንድ ሺ ኪሎ ሜትር ጉዞ በአንድ እርምጃ ይጀመራል ነው የሚሉት:: የምንጀምረው እርምጃ ግን በትክክለኛ አቅጣጫ መሆነ አለበት:: በተሳሳተ አቅጣጫ ጉዞ ከተጀመረ አለመድረስ ብቻ አይደለም ያለው አደጋ::

Monday, June 13, 2011

የልብ እግር ሲሰበር ...ሲሽር

የልብ እግር ሲሰበር
ዓላማ ፣ ተስፋ ፣
ፍላጎት ፣ ምኞት... ሀሴት
ሕይወት አልባ ይሆናሉ::
ሲሽር እንደ አዲስ ነብስ ይዘራሉ ::
ህብረት ይፈጥራሉ
መሰናክል ይዘላሉ ::
ግና ሰባራ ልብ የሚያራምደው
...ወጌሻው
የጽናት እና የእምነት ትብብር ነው ::

ሰኔ 7, 2003,
ቶሮንቶ

Tuesday, March 15, 2011

Rethinking the notion of “self-determination”

The notion of “self-determination” was projected as an important manifestation of political consciousness in Ethiopian politics immediately before and/or following the Ethiopian revolution in 1974. Yet, a closer critical look of the principle reveals a different picture. The notion of “self-determination” ,as it relates to Ethiopian politics, rather tells a story of political unconsciousness and consequent adoption of a reductionist view of “self.” In a collectivist society, identity – in this case “self”- is a social construction as much as it is a political one,if not more.Apart from unconsciousness,  mystification of the notion of “self-determination”  in total disregard to the need for an objective inquiry of  the Ethiopian situation ( historical,political, social and cultural, among others) is in part indicative of over-receptiveness of concepts from the outside world without questioning their relevance in a collective society like Ethiopia. In fact, even the issue of receptiveness could be seen as an offshoot of political unconsciousness. 

This short article represents neither an exhaustive nor definitive view of “self-determination” in the context of Ethiopia. It does, however, represent a call to fellow Ethiopians –especially those who bought the idea as a sacred political creed and who are selling it in the same sense – to question its relevance in light of objective inquiry of the Ethiopian situation. I argue that the notion of “self-determination” is over-politicized, and wrongly, at the expense of collective values (social and cultural, among others) that shaped collective identity. Identity, to a great extent, is supposed to be a social construction, in my view, –not a political manufacture from exotic political concepts. The conception of “self” is taken in its absolutist and reductionist form among those who dared to craft identity out of political opposition. Embedded in the notion of “self-determination” is exclusive justice which neither desirable nor possible. 

Why I am questioning the notion of “Self- determination”:

In one of my undergraduate courses, “ The Global South”, the professor posed the question “ Is international law an instrument of domination?” The question was so interesting to me so much so that I asked the professor if I can write one of my research papers for the course on that same question. Not that I had good understanding or previous reading on the topic. It was out of mere curiosity to challenge my own speculative “yes” answer and have a closer look, and understand intuitive critical and negative attitude ,which I developed, towards the “international community” on grounds of the way the “international community” handles issues in the international arena: inconsistency, cynicism, hypocrisy, "humanitarian wars" and what have you.   For some reason, I believed that “international law” is as mediocre as the “international community” and my belief is informed by the political experience of my people. Tracing the origin of international law could have, I believed, given a clue to address the question as to whether international law is "an instrument of domination "or not?  

Preliminary readings which I did for the paper were not that useful. Most of the materials I consulted were of Eurocentric origin. Consequently, they  tend to have a deferential view of “international law.” I discovered crucial clue related to my question only, of my readings, in the work of Karl Polanyi’s - “Great Transformation.” At one point, there seems to be a suggestion that the origin of “international law” was the 'international system' which was entirely a European enterprise. It was meant to maintain a balance of power between European powers by way of averting and handling possible conflicts - you may call it the "league of nations" of the then Europe. Even North America was not part of the system.

My next question was whether "international law" was relevant vis-à-vis defending sovereignty of states and peoples at the time they were subject to colonial wars of conquest and treaties of treachery. From the outset, I happened to learn that the contribution of African and other third world scholars to international law was meager, if not nonexistent, in the formative stage of 'international law.' Contributions from TWAIL is a post-colonial phenomenon. And I am aware that a body of law is supposed to reflect moral codes, norms and views of the society for which it is intended to serve. In that regard, international law was not international enough. Far from providing legal protection to peoples in Africa and elsewhere, 'international law' provided legitimacy and justification for colonial powers in their occupations of territories in Africa. 

The existence of legal principles in “international law” that sound like tools of domination and oppression ,seen from the trajectories of colonized countries ,is another reason to doubt “international law.” Concepts like “Terra nullius,” and the notion of “positivism and positivist interpretation” could be cited as an example. On the basis of these clues, who would not presume that the partition of Africa by European powers with the motive of “civilizing mission” was endorsed by “International law” ,at least by omission.

All is not history though. There is a subtle continuity. Although it is difficult to make categorical assertion on that, even neo-positivism is not immune from bias of the powerful countries. Neo-liberalism composed a propaganda song that “sovereignty” – which was once a cardinal principle in relation to the independence of peoples and nations in international law–is a thing of the past. Obviously, the intention is to facilitate mobility and expansion of capital and exploitation in a more subtle way, unlike the era of colonization which was through wars of conquest. My point is not about neo-liberalism. I am trying to substantiate the point that international law simply served as interpretive frame work to justify domination in colonial era and the world is not immune from new forms exploitation and domination that could appear under the guise of “international law.”  I suppose reference to international laws in the realms of trade law could give a clue on that. The notion of “self-determination” ,which is now part of the international law, could serve that purpose too.

Rethinking the notion of “self-determination”

The principle of “self-determination” was introduced to international law during decolonization era. It appears the case that the genesis of concept has a root from leftist political thinking. Probably the principle initially came to be part of international law in part due to the ideological war between the East and the West blocs, and in part  due to the appeal of the concept for colonized peoples. Whatever the case is, in light of the struggle against colonialism, and in light of the fact that the struggle was between powerful colonizing countries of Europe on the one hand, and the colonized people of Africa ,which  were subjected to exploitation and inhuman treatment* in their own country , on the other – I would say the notion of “self-determination” was relevant back then. In this case the concept “self” is not suffering from absolutist and reductionist view. Because in the concept “self” the embedded “other” is clear. Indeed, the other is entirely different from  the perceived “self” for historical, political, cultural, economic and social reasons. 

The principle tends to take an absolutist turn when it is applied within a country- especially in Africa. Unfortunately, the principle got strong political currency in Ethiopia immediately before and/or after the 1974 revolution. The political movement of the 70’s in Ethiopia was influenced not only by leftist thinking but also the anti-colonial struggles in Africa in the 60’s and 70’s. Scholarship students from African countries at AAU are said to have their own role in shaping the political "conscious" of Ethiopian students, a social group which was to emerge as political activist.** however, the consciousness is only apparent, not real. Clearly, there was some unconsciousness within the new political 'consciousness'. The notion of “self-determination” is a good example to demonstrate that. Yet, it was not political unconsciousness per se that made the notion of “self-determination” a strong political currency in the politics of the 70’s. Even a fairly little exposure to the political writings of the 70’s in Ethiopia seems to suggest that the youth was highly politicized – and political mobilization was highly competitive. Based on circumstantial evidence, I tend to think that the notion of “self-determination” provided mobilization convenience for young political activists. Apparently, mobilization convenience provided by the “notion of self-determination” made political activists forget the fact that oppression and exploitation was not exclusive in feudal Ethiopia. It was rather a shared experience. 

In addition to political unconsciousness ,and mobilization convenience that the notion of “self-determination” rendered,  ideological and political values  of the principle in the eyes of external forces (forces which have the aspiration to destabilize and weaken Ethiopia for Ideological  and/or historical reasons) added value to the currency of the principle as a means to garner support from the outside world. Some Arab nations which seemed to have envisaged interest in a destabilized Ethiopia provided diplomatic, financial and military support for the “liberation fronts” which emerged out of the student movements and were waging a guerrilla war against the provisional military government. Western countries in their own right have a feud with the military government due to its ideological orientation and opted for supporting “liberation fronts.” Technically, that was like recognizing the principle of “self-determination” in the Ethiopian situations. Some “scholars” like David Basilson went to the extent of openly portraying Ethiopia as a colonial power. Apparently, the liberation front’s endorsement of colonial thesis was informed by readings from the writings and commentaries of David Basilson. So apart from mobilization convenience at home, the politics of “self-determination” helped gain acceptance and legitimacy by foreign powers.

The colonial thesis was utterly nonsense. In connection with this, the problem related to “self-determination” in Ethiopia primarily emanated from mistaking power struggle between local feudal lords and campaigns to unify the country with colonial wars of conquest. There was, so to speak, no such thing as election campaign and election in feudal Ethiopia. The way to assume power –like any feudal societies in Europe and the rest of pre-colonial Africa– was through feudal war. On top of that, Ethiopia itself survived a colonial war of conquest –and that was achieved with the participation of all the contending feudal lords and their armies. On the contrary, colonial wars of conquest were essentially capitalistic enterprises. They were about expanding capital by way of creating a resource market in addition to imperialistic tendency. As a result of the process, resources were looted from Africa and transferred to the metropolitan. As people,  Africans lost dignity-in their own country. The economic, social and cultural policies that colonial powers pursued in colonized African countries were devastating to the Africa. So the champions of “self-determination” in Ethiopia clearly mistook the latter for the former. This is one of the unconsciousness.

The notion of “self” was taken in its reductionist sense and runs a linguistic line more than anything else. But clearly “self” is more than language. “Self” is a product of other cultural ,and social interactions too. Assertions of cultural domination are problematic too for the simple reason that there have been multi-directional cultural assimilation.  These assimilation and intermarriages could not be discounted when defining “self.” All the “cultures” in Ethiopia are collective in nature. And there have been interchanges of cultural values even from one collectivist cultural setting to the other. Something had been given and something had been taken. This is indicative of the fact that “the notion of “self" should be understood more broadly than it is understood now, and that it is significantly a social and cultural product rather than a political one - in the context of Ethiopia. This is the reality was not given a room and in fact casted aside.

Political activists who picked up the notion of “self-determination” for mobilization convenience purpose simply mined a justification for the absolutist, reductionist and exclusive notion of “self” in the politics of feudal Ethiopia. They failed to see that the colonial type of social and cultural interaction was entirely different. The Zimbabweans were segregated in their own country- and there was a legal and institutional frame work to undertake segregation by the white minority rule from Europe- the “other”. South Africans have a similar, perhaps worse by any measure, experience. Although a little off topic, the experiences of blacks in North America – in an allegedly "liberal and free society"- could offer another comparative framework. Yes, the North American case was not a purely colonial case. Yet, the experiences of blacks are comparable to the experiences of Africans under minority rule of the “other” – colonial powers. In the first place they were "stolen"  from their origin.“Slaves” from Africa were made to entirely forget their cultural values- and they were made to live under institutionalized racial segregation. The dream of Martin Luther king was-literally-the end of racial segregation. I am not sure if Martin Luther King envisaged of more. What one finds when digging Ethiopian feudal politics is political marriages, assimilation, and a shared culture. 

In light of these experiences what happened in feudal Ethiopia represent nothing other than the low political stage of development of the feudalism. And all parts of Ethiopia experienced feudal rule under their respective feudal lords. I am of the view that the feudal experience should not be an excuse to entrench an absolutist view of “self.” It is also wrong to entrench exclusive sense of justice in a collective society. The notion of “self-determination” , as advocated by Ethiopian politicians, is about excluding perceived “other” rather than bringing about justice that serves a collective purpose.

Besides, no society lived harmoniously and without conflict throughout history as conflict is an integral part of human life and it exists at different levels. In that case, even the politics of “self-determination” is not a guarantee for a just and harmonious society. The guarantee for a relatively just society is the creation of a strong and inclusive notion of justice by way of transcending an incomplete and wrong conception of “self.” All the components of “self” matter. Language is just one component. I strongly believe that the notion of “self-determination” is neither desirable nor possible. It just deepens ethnic divide which is not constructive at all. This is the challenge that comes with unexamined notion of "self" and "self-determination."  It’s a challenge not just for Ethiopia– but for Africa as well.

The irony is that while political activists in a country like Ethiopia –and other parts of Africa as well- take an absolutist view of “self” and consider a component of “self” as the “other”, the real “other” – the historical “other” making a different move in a more sophisticated form and is working in multifarious ways to demolish collectivist cultures in Africa and elsewhere so as to create a consumer and a resource market. Contemporary ruling classes in Africa are connecting with them and introducing their values. Globalization is essentailly a manifestation of that project. It represent a clear threat to the real “self.” It is not the component of “self” that represents danger to “self.” It is the “other.” It is high time to give the notion of “self-determination” a second thought.



********************** The End *****************

Notes:

*To get a sense of human rights violation in Africa, see Makau Mutua’s,Harvard scholar from kenaya, interesting article the “ Savage, victim and Saviour: methphors of human rights.” Through this article, I was able to see “self” and “other.” Also it can help to see anachronism by champions of absolutist “self” who mistook feudalism with capitalism.

** Among others, Literatures like Andargachew Asegid’s “ Bachir Yetekeche Rezim Guzo” and “ Yidres le bale Tariku” are essential to analyze the politics of the 70’s in Ethiopia

Monday, March 7, 2011

ሚስጥረ ልብ !

እንደ ባሊና ኳስ ልብ እየነጠረ
ከሰው አልመከረ ;
እግር አልተነሳ ; ወሰን ተሻገረ ::

""ምን ለመሆን ነው
የሰው ነገር ...የሰው
ሲሆን እያወከው ?! ""
ብየ ብጠይቀው
ዝም አይነቅ ዝም !
መንጠሩን ግን አላቆመም ::

ነጥሮ ነጥሮ እንደገና መሬት ደረሰ
መሬቱ ላይ መሬት ሆኖ ቀረ ዝምታ ነገሰ
ትንሽ ቆይቶ ደሞ ተላወሰ
የታየውን ....ተነፈሰ

"" እንደኖርኩት ...እንደማውቀው
ልብ በዋዛ አይመታም
ወደላይ አይጉንም
መሬት ላይ አይነጥርም ::
እንዲህ የሚጉነው
እንዲህ የሚነጥረው
የመታው ቢለይ ነው !""
ሲል ቢነግረኝ
የልብ ንጥረቱ ና ስደቱ ገባኝ ::

ከስደትም የተሰደደ ልብን ለሚያውቁ

የካቲት 27, 2003,ቶሮንቶ

Monday, February 28, 2011

የዳቦ ወይስ የፖለቲካ ጥያቄ?

ድሮ ኮተቤ ኮሌጅ ስማር የረሀብ አድማ ተደርጎ ነበር:: በጊዜው የነበሩት የተማሪዎች መማክርት አባላት የህዋሀት አባልና አንዳንዶቹም ታጋይ የነበሩ ናቸው:: በደንብ አስታውሳለሁ እነዚህ አመራሮች የተሰበሰበውን ተማሪ የተጀመረው አድማ መቶ በመቶ ከምግብ አቅርቦት ጥራት ጋር የተያያዘ እንደሆነ እና የፖለቲካ ጥያቄ እንዳልሆነ አጽኖት ሰጥተው ""ፖለቲካ ከተነሳ በየለሁበትም""አይነት መንፈስ ተማሪውን ያስጠነቅቁ ነበር:: ከዚያም መፈክር ይጻፍ ተብሎ በአራት ቋንቋ ተጻፈ:: የማስታውሳቸው ""ረሀብ ጊዜ አይህብን"" ""ጋፊን ኬኛ ጋፊ እኛታቲ"" ""ጥያቄያችን የዳቦ ነው"" እና ""we demand bread"" ነበሩበት:: እውነት ለመናገር የዳቦ ችግር አልነበረም:: በእኛ ሀገር ስታንዳርድም ይቀርብልን የነበረው ምግብ አድማ የሚያስመታ አልነበረም:: እርግጥ ነው የካምፓስ ምግብ የጣዕም ችግር አለበት:: እሱ ደሞ ሀገራችን ደሀ እንደመሆኗ አድማ የሚያስመታ ጉዳይ አልነበረም:: በኍላ ሲገባኝ የምግብ ጥራት እና ""ጥያቄያችን የዳቦ ነው"" ጩኽት ትክክለኛ ምክንያት አልነበረም:: ጥያቄያቺን ""የፖለቲካ አይደለም"" የሚለውም ሀሳብ እንደዚያው::
ለአድማ ያነሳሳው ትክክለኛ ጉዳይ የታፈነ የማህበራዊ እና የፖለቲካ ችግር ነበር::

በ1992 ዓመተ ምህረትም አገሪቱን ሊያነቃንቅ የሞከረ የተማሪዎች አመጽ ተከስቶ ነበር:: የህዋሀት መንግስት ከ40 በላይ ንጹሀን ዜጎችን ገድሎበታል:: የዚህኛውም አመጽ ጥያቄ እንዲሁ ዙሪያ ጥምጥም ነበር:: ""የአካዳሚክ ነጻነት"" ጥያቄ ነበር በዋነኛነት የተስተጋባው:: ወያኔም እንደለመደው ያለ እፍረት ""ጥያቄው የአካዳሚክ ጥያቄ አይደለም:: የፖለቲካ ለውጥ ሊያመጡ የፈለጉ ኃይሎች ናቸው ያንቀሳቀሱት"" የሚል አስተሳሰብ ይዞ ተማሪውን የዘር ፖለቲካ በማራገብ ሊከፋፍለው ሞከረ:: ምናልባት ብዙዎቹ የፌስ ቡክ ጓደኞቼ የዚያ እንቅስቃሴ ቀጥተኛ ተሳታፊ የነበሩ በመሆናቸው ከላይ ያልኩትን ነገር እንደሚያስታውሱት እገምታለሁ::

ታዲያ ዛሬም ድረስ የማይገባኝ ነገር የአንድ ሀገር የዪኒቨርሲቲ ተማሪዎች ; በመሰረተ ሀሳብ ደረጃ የሀገሪቱ የወደፊት ተስፋ እና ሀገር ተረካቢ እንደመሆናቸው መጠን ቀጥተኛ የሆነ የፖለቲካ ጥያቄ መጠየቅ የማይፈቀድላቸው ለምንድን ነው?? እንደ ዜጋ የፖለቲካ መብት የላቸውም ወይ??

የኮተቤው የተማሪዎች እንቅስቃሴ ሲደረግ ወያኔ በጎጃም ገበሬዎች ላይ ይሄ ነው የማይባል ከፍተኛ በደል አድርሶባቸው ስሞታ ለማሰማት አዲስባ ድረስ የመጡበት ሁኔታ ነበር:: ተማሪው በገበሬው ላይ በተደረገው ነገር ተቃውሞን እና ሀሳቡን እንኳን እንዲገልጽ አልተፈቀደለትም ነበር:: ለምን? "" የፖለቲካ ጥያቄ"" ስለሆነ::

በተመሳሳይ ሁኔታ የ1992ም የአዲስ አበባ ዪኒቨርስቲ ተማሪዎች ""የአካዳሚክ ነጻነት"" እንቅስቃሴ ከመደረጉ ትንሽ ቀደም ብሎ ወያኔ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል በተለይም በኦሮሚያም በዜጎች ላይ ሽብር ይነዛ ነበር:: ዜጎች የኦነግ አባል ናችሁ እየተባሉ ቁም ስቅል ያዮ የነበረበት ጊዜ ነበረ:: ከኦሮሚያ አካባቢ የመጡ ተማሪዎች ተቃውሟቸውን ለማሰማት እንዴ በዮኒቨርሲቲው ጊቢ እስቅስቃሴ ሲያደርጉ የአጋዚ ሰራዊት በጨለማ ገብቶ የህዋሀት አባል ተማሪዎች መሪ ሆነው የተማሪ ወታወቂያ እየታየ ተማሪዎች ወደ እስር ተግዘዋል:: እንዲህ እንዲህ አይነት ወያኔ የሚወስዳቸው የፖለቲካ አካሄዶች ያለጥርጥር በወያኔ ፖለቲካ ላይ ጥያቄ ያስነሳሉ:: በሌላ በኩል የዮኒቨርስቲ ተማሪዎች የፖለቲካ ጥያቄ እንዲጠይቁ አይፈቀድላቸውም:: ""ጥያቄያችን የዳቦ ነው"" እየተባለ እስከመቼ ነው የሚኖረው?? የነገ ተስፋችን በማን እጂ ነው ያለው??


ሰሞኑን የግብጽ እና የቱኒዚያ ወጣቶች አብዮት አካሔዱ ብሎ የወያኔ መንግስት ሺብር ስለገባው ; ወላጆችን ሰብስቦ ልጆቻችሁን ያዙ እንዳለ ሰምተናል:: ሚገርመው ወላጆች ልጆቻቸውን የሚይዙት እኮ የፖለቲካ ጥያቄ እንዳያነሱ ነው:: በሌላ በኩል ይሄው መንግስት የኢትዮጵያ ወጣቶችን በተለያየ መልኩ እያደነዘዘ የፖለቲካ ድንፈፍ ሊያደርጋቸው እየሞከረ ነው::ቅጥ ያጣ ነቀት ማለት ይሄ ነው:: በወያኔ መንግስት ላይ ወጣቶች ሊያነሷቸው የሚገቡ ብዙ ጥያቄዎች አሉ::

እኔ ግን በዋነኛነት የምጠይቀው የህወሀት መንግስት የኢትዮጵያን ወጣቶች በስራ እድል እና በጥቅማጥቅም በመያዝ ታማኝ የስርዓቱ ተገዢዎች እንዲሆኑ የወሰደው እርምጃ ነው:: ኢትዮጵያውያን ዜጎች የትምህርት ደረጃቸው በሚፈቅድላቸው መጠን የመንግስት የስራ ዕድል የማግኘት መብት አላቸው:: ይህንን ህጋዊ መብታቸውን ዘንግተው ለስራ እድል ተብሎ የፖለቲካ እምነታቸውን መቸርቸር እና የማያምኑበትን የፖለቲካ እሳቤ እንዲያራምዱ መደረግ የለባቸውም:: የህዋሀት መንግስት በጉልበት እያስተዳደረው ባለው የኢትዮጵያ ሀብት የፖለቲካ መነገጃ የስራ ዕድል መፍጠሩ በኢትዮጵያውያን ወጣቶች እንደውለታ መታየት የለበትም :!: ህዋሀት ከኪሱ የከፈለበት ጉዳይ የለም:: እንደውም ባለፈው ከአቶ ስብሀት ነጋ በቪኦኤ እንደሰማነው ህዋሀት የትየለሌ የሆነ ሀብት እንዳጋበሰ ነው:: ያ ተረስቶ ጭራሽ ለኢትዮጵያውያን ውለታ እንዳደረገ ማሰብ ምን ያህል የፖለቲካ ድንዝዝነት እንደነገሰ ብቻ ነው የሚያሳየው::

እስከዛሬ ድረስ ቀጥተኛ የሆነ የፖለቲካ ጥያቄ ባለመጠየቅ ; የህዋሀት መንግስት የሀገሪቱን ሀብት እና ንብረት እንደፈለገው ሲያደርገው በመቆየቱ ህዋሀት የኢትዮጵያውያን ወጣቶች ውለታ አለበት:: ከገባው:: ህዋሀት ከስልጣን ከወረደ የተገኘው የስራ ዕድል ይጠፋል ብሎ ማሰብ የፖለቲካ ሞኝነትም ነው:: የኢትዮጵያ ወጣት ተስፋ ነገውን በእጁ በማስገባት እና ባለማስገባት ላይ የተመሰረተ ነው:: በህዋህት የፖለቲካ ዳረጎት አይደለም!! ህዋሀት ከስልጣን ቢሽቀነጠር ቀን የሚጭልምበት ኢትዮጵያዊ አይኖርም:: ከጨለመ የሚጭልመው ለራሱ ለህዋህት ብቻ ነው:: የፖለቲካ ለውጥ ደሞ ያስፈልጋል::ሀያ አመት ሙሉ የዘር ነጋሪት እየመታ ""በብሄር ብሄረሰቦች"" የማደናገሪያ ስልት የፖለቲካ ስልጣን በማያፈናፍን ሁኔታ ይዞ ሲዘርፍ ከኖረ የፖለቲካ ቡድን ነጻ መውጣት በራሱ ትልቅ ስኬት ነው:: ነጻነት የሌለው ወጣት ተስፋ አለኝ ሊል አይችልም! የደስታ ሆነ የስኬት; የተስፋ መሰረቱ ነጻነት ነው:: ነጻነት የሌለው ሕብረተስብ የትም ሊደርስ አይችልም::

Tuesday, February 15, 2011

ወይ ቫለንታይን?!

ሰው የመሆን ትርጉም የሚያጎላው ማሰብ እና ማገናዘብ መቻል ነው:: ከሌላው ፍጥረት የምንለይበትም ምክንያትም ይሄው ነው:: የሚያስብ እና የሚያገናዝብ ሰው ደሞ እንዳረጉት አይሆነም:: ይጠይቃል:: ""ለምን?"" ይላል:: ባለፈው በዚሁ በፌስ ብክ ፔጄ ላይ "" ዘመን የሰጠን እና የወሰደብን ነገር ምንድን ነው?"" የሚል የመወያያ ርዕስ አንስቼ የፌስ ቡክ ጓደኞች የጠበኩትን ያህል መልስ አልሰጡበትም:: እንደውም ምንም አልመለሱም:: የግብጽ ወጣቶች ሰሞኑን ትንግርት አሳይተውናል:: ዘመናዊነት የሰጣቸውን የቴክኖሎጂ ጥበብ -ኢንተርኔትን ተጠቅመው - አገሬን እወዳለሁ ይል የነበረ መሪያቸው ( ሙባረክ) የወሰደባቸውን ነጻነት በጽናት ታግለው አስመልሰውታል:: ሙባረክ የወሰደባቸውንም የትየለሌ ገንዝብ ለማስመለስ በዝግጂት ላይ ናቸው:: የተለያዩ የህብረተስብ ክፍሎች የሚገባቸውን መብት እንዲያገኙም ትግላቸውን ቀጥለዋል:: የግብጽ የለውጥ አብዮት አልቆአል ማለት አይደለም:: ከሁኔታቸው እንደተረዳሁት ትግሉን እዚህ ቦታ ላይ በቁሙ የሚጥሉትም አይመስለኝም:: እንዳልሆነ ሆኖ ሊሰበር ስለሚችል:: የግብጽ ወጣቶች የነጻነት ትግል መንፈስ ግን መንፈሳዊ ቅናት ያሳድራል:: የግብጽ ወጣቶች በዘመናቸው ላይ ተጽዕኖ ለማድረግ ሞክረዋል:: ዘመን እስከመጨረሻው ባሪያ እንዲያደርጋቸው አልፈቀዱለትም:: የግብጽ ወጣቶች ይሄንን ሁሉ ሲያደርጉ ኢትዮጵያ ውስጥ የቫለንታይንን ቀን ለማክበር በሬዲዮ እና በቴሌቭዥን ነጋሪት ይጎሰም ነበር አሉ:: አዲስ ነገር ኦንላይን ላይ ስለ ቫለንታይን ቀን የተጻፈውን አንብቤ በጣም ተገርሜአለሁ::
ወጣቱ እንደዚህ እንደዚህ አይነት -ከልብ ሆነው ሲያስቡአቸው ትርጉም የማይሰጡን አውሮፖዊ አስተሳሰቦች እና ባህሎች የሙጥኝ እያለ በያዘ ቁጥር; ትርጉም ያላቸውን እንደ ነጻነት ያሉ እና የሀገር ጉዳዮችን ቸል እያለ እና ከናካቴውም እየረሳ ይመጣል:: በመርህ ደረጃ ስናየው ፍቅር የበለጸጉ ሀገሮች ያወጡት ኮንቬንሺናል ቀን ያስፈልገዋል ወይ የሚለው ራሱ አንድ ጥያቄ ነው:: በባህልም በእምነትም እንደማውቀው ፍቅር የዕለት ተዕለት ጉዳይ ነው:: ያለፍቅር አይዋልም አይታደርም:: በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባለ ማህበረሰብ ውስጥ:: እርግጥ ነው ስጦታ ፍቅርን ይገልጽ ይሆናል:: ሀዲስ አለማየሁም ""ለሚወዱት ሰው የሚደረግ ስጦታ ከሚቀበለው ሰው ይልቅ የሚሰጠውን ሰው ልብ የበለጠ ያስደስታል"" ብለው ጽፈዋል:: ያስማማል:: ጥያቄው ግን የፍቅር መግለጫ ስጦታ ለመለዋለጥ እና ፍቅርን ለመግለጽ February 14 አይዲያል ነው ያለው ማን ነው? የቫለንታይንን ቀን myth የፈጠረው ማን ነው? ዓላማውስ ምንድን ነው ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል:: ስፔሻል የሆነ ቀን ከሆነ የሚፈለገው ""በኮንቬንሽን ደረጃ የሚከበርን ቀን የወል ይሆን እንደሁ እንጂ የግል ሊሆን አይችልም::
ከተጨባጭነት ስናየው ደሞ አውሮፖዎቹ እና አሜሪካዎቹ (ሌሎችም የበለጽጉ የእስያ ሀገሮች) የቫለንታይንን ቀን ቢያከብሩም የኢኮኖሚ ሁኔታቸው ይፈቅድላቸውል:: ጦሙን የሚያድር እና ስራ አጥ ማህበረሰብ በበዛበት ምድር ከአውሮፓዎቹ እና ከሌሎች ከሞላላቸው ሀገሮች እኩል የምናብ ቫለንታይንን የሚከበርበት ምክንያቱ ሊገባኝ አልቻለም:: ከላይ የጠቀስኳቸው ማህበረሰቦች ወጣቶች በተወሰነ መልኩ ምርታማ ናቸው:: ከዚያም ባለፈ የት ገባችሁ የት ወጣችሁ ምን አሰባችሁ የሚላቸው ጉልበተኛ መንግስት የለባቸውም:: የመንቃት እና ያለመንቃት ዕድሉ ያለው በእጃቸው ነው:: እኛ ጋር ያለው ነባራዊ ሁኔታ ሌላ:: ባለፈው ሳምንት ሀገር ቤት ስልክ ደውየ የማልጠብቀው የቅርብ ሰው ""የወያኔነት"" ፎርም ሞላሁ አለኝ:: ለምን እንደዛ ሆነ ብየ ስጠይቅ በቃ እንደዛ ካልሆነ ተምሮ ስራ ማግኘት አልተቻለም የሚል መልስ ነው ያገኘሁት:: የአንድ ሀገር ወጣት በዜግነቱ እና በችሎታው የስራ ዕድል ለማግኘት የማይችልበት ዘመን ላይ ተደርሷል ማለት ነው:: ግፈኛ የሚባለውን የደርግ አገዛዝ በደንብ አድርጌ አስታውሰዋለሁ ስዎች ስራ ለመያዝ የደርግ ፓለቲካ ደጋፊ መሆን እንዳለባቸው አላስታውስም:: አሁን ያለው መንግስት ግን በግልጽ ስራ አጥነትን ራሱ አስፋፍቶ ; የስራ ዐድልን ደሞ የፓለቲካ መነገጃ አደረገው:: የደርግ መንግስት ደሀ ነበረ:: የመንግስት ድርጂቶች እንደነበሩ አስታውሳለሁ:: ንብረትነቱ የደርግ ፖርቲ የሆነ የንግድ ተቋም እንደነበረ ግን አላስታውስም:: አንድ ጊዜ አቶ ስብሀት ነጋ የሚባሉት የህዋሀት ሰው በአሜሪካ ድምጽ የአማርኛ አገልግሎት ላይ እንደተናገሩት የህዋህት ፓርቲ እጂግ በጣም ሀብታም ነው ; መገመትም ያስቸግራል ነው ያሉት:: ይሄ ሁሉ ሀብት የተገኘው ደሞ በዛች በደሀ ሀገር ስም እና ከዛች ከደሀ ሀገርም ነው:: ስራ አጥነት ግን ተንሰራፍቷል:: ኢትዮጵያን የሚመራው የወያኔ/ህዋሀት መንግስት ደሞ ዜጎች ስራ ለማግኘት እንደ ዜጋ እንደ ኢትዮጵያዊ ሳይሆን ; የህዋሀት እና እህት ድርጂቶች ፓርቲ አባል መሆን እንደሚጠበቅባቸው እየነገረ ስራ ሲሰጥ ; ወጣቱ ህዋሀት/ኢሀዴግን እንደባለውለታ ሁሉ ያይ ጀመር አሉ:: ሚያሳዝነው ረሀቡንም ስራ አጥነቱንም የፈጠረው ( ቢያንስ ያስፋፋው) ሀዋሀት/ኢሀዴግ ሆኖ ሳለ; ይሔው ፖርቲ በፖለቲካ ወገንተኝነት መመዘኛ የስራ ሰጪ ሲሆን በጎ አድራጊ መንግስት ሁሉ ሆኖ ቁጭ አለ:: እንዳረጉት መሆን ማለት ይሄ ነው:: ይሄንን ለማሰብ ያልቻን ወይ ያልፈለግን ደርሰን ከሞላላቸው እኩል ""ቫለንታይን" ላይ ስንጠላጠል የሚገም ነገር ነው::

ዛሬ የቫለንታይንን ቀን ምክንያት አድርጌ አነሳሁት እንጂ የፈረንጆች አዲስ ዓመት ሲከበር አዲስ አበባ ሻራተን ጠጠር መጣያ እስከሚጠፋ ሰው ሞልቶ አበሻው የፈረንጆችን በዓል ቁጥር እይቆጠረ አክብሯል:: ""የኢትዮጵያ ቴሌቭዢንም"" ስርጭቱን በቀጥታ አስተላልፏል:: የምናስብ ትውልዶች ነን ለማለት ማስረጃ ማግኘት ሁሉ እየከበደኝ ነው:: ያ ሁሉ ነገር ሻራተን አዲስ ቢቀርም ኖሮ እኮ አንድ ነገር ነበር:: ሌላኛው ያልገባው ወጣት እንዲጓጓለት ተደርጎ በቀጥታ በቴሌቭዥን መተላለፉ ነው የሚያስቆጨው:: በየገጠሩ እና በክፍለ ሀገር ከተሞች ያለው ወጣት ያንን እያየ ኢትዮጵያ "አድጋለች"" እያለ እንዲሳሳት እና ማንነቱ እንዲወናበድበት እየተደረገ ነው ያለው:: ከታች ያለውን ክሊፕ ተመልከቱ::

http://www.youtube.com/watch?v=VceDMjlfLdQ

የኢትዮጵያውይንም ገና እየተረሳ "' x-mass'" ላይ ትኩረት እየተሰጠ እንደመጣ ነው የሚሰማው:: ትውልዳችንን እንዳረጉት እየሆነ ነው:: የሚያደርጉት ደሞ ራሱን ሳይሆን ሌላ አይነት::እየሆነ ያለውን ነገር ሁሉ ዝም ብለን በዘመን ተጽዕኖ ሂሳብ መያዝ አለብን? ነው ጠንከር ያለ ነገር አለ?? ማነው እየመራን ያለው? ወዴት ነው እየተመራን ያለነው? አሁን የተያዘው አካሄድስ ያስፈልገናል ወይ? የኢትዮጵያ ባህል አደንዛዥ ነው ጎታች ነው ...ምናምን ምናምን እየተባለ ሌላ አንደንዛዥ የሰው ሀገር ባህል እና አስተሳሰብ ያስፈልገናል ወይ? በእርግጥ የህይወት ትርጉሙ ምንድን ነው? ማንስ ነው የሚተረጉምልን? የደስታ ምንጩ ምንድን ነው?

በዚህ ጉዳይ ላይ ሀሳብ ብንለዋወጥ በጣም ደስ ይለኛል ::

Thursday, February 3, 2011

"I blow out first ..."

This evening I happened to listen to a conversation between two teenage boys in men's locker room in a gym. I will refer to them as B1 and B2.

B1: listen I've a question. My girl friend blow out a lot. Do you argue with your girlfriend very often?
B2: We do.
B1: like on big...big issues?
B2: We even argue on every little issues
B1: Who blows out first?
B2: depends. If I didn't eat I blow out first. lol

Saturday, January 29, 2011

እስከመቼ?!

ተሸክሞ የብሶት ቁልል
ችጋርና ርሀብ ቤቱን ሰርቶ
ቁራሽ ምኞት ሆኖ አርፎ
በፈረቃ እየተበላ ስንቱ
በየቤቱ ራሱን ስቶ
ቁራሽ ፍለጋ ተከልቶ
ቀየውን መንደሩን ትቶ;
ከሁለት ያጣ እንዲሉ
ቁራሹም ጠፍቶ ላመሉ
ቀየውንም ቁራሹንም እየተራበ
ጉደኛ አሳዳሪ...
""ዕድገት"" አለ እያለ ከበሮ ደረበ::

"" ህዳሔ አለ ...ዕድገት አለ
አስፋልት ተነጠፈ
ጥርጊያ መንገድ ተደለደለ
ለዕድገት ተብሎ..
ለአረቡ; ለቻይናው; ለህንዱ መሬት ታደለ
ዕድገት አለ:: ""

እንዲህ አይነት ፌዝ እየሰማ
አበሽ ልቡ እየደማ
በረሀብ የሚፈጀው
ረሀብ እና ባርነት ያደረጀ 'ሚታገሰው
እስከመቼ ነው?!

የ""አትንኩኝ"" ባይነት መንፈስ
ነጻነት ባበቀለበት ምድር
ዛሬ "አትንኩኙን" ማን ቀጠፈው
ማን ቀላቀለበት ከአፈር::

ምነው አበሽ ዝምታ አበዛ አንገቱን ሰበረ
"'ከመናገር ደጃዝማቺነት ይቀራል"" ተረስቶ
ስለምን ለዘራፊ አሳዳሪ አቀረቀረ??

ኧረ እንደልማድህ አበሽ
ኑር እንደ አባት አደሩ
ችጋር; ባርነት ለሚደግስ
እስከመቼ እሺሩሩ??



ጥር 2003 ቶሮንቶ

Monday, January 24, 2011

Leave the Ethiopian God alone

This was a response to a discussio on facebook

In light of the experience of France and other European countries, a major change, (I am avoiding to use the terminology revolution as there is a lot of stigma attached to it,) is preceded by a period of intellectual discourse. The discourse is meant to understand the kind of change needed and explore impediments to effect those changes. I salute you for taking the initiative to trigger discussion on this matter. Indeed it is high time to question as to what stands between the need for freedom and the apparent success of dictatorship to avert change in Ethiopia.


For me,the problem has a lot to do with consciousness (in its social and political form). Yet, you were bold enough to throw the cross on the “Ethiopian God” and the Ethiopian church as major factors affecting change – change towards Freedom. If I capture you correctly, your premise runs something like “Ethiopia has been in prison for thousands of years” and you advanced the argument that “ Ethiopia’s true imprisoner [captor] is her own creation, her own God.” And you concluded by suggesting creation of a new God.

To begin with I don’t agree with the assertion that "Ethiopia has been in prison for thousands of years." What exactly is prison? It sounds that by prison you are making reference to Ethiopian Christianity. Christianity is not a faith that Ethiopia created. Rather Ethiopia took Christianity very seriously. Do you know of any society that is not influenced by this or that form of faith/religion?  Are you asserting Ethiopia's imprisonment on the basis of modern political thinking? If that is the case, which empire and/or nation in the world could be free from this allegation? Which country was not in "prison" for millennium? The politics of the past –especially that of thousands of yearscould/should not be analyzed on the basis of “modern” political thinking. Pre-modern Europe was conservative, monarchical and Christian too. The Manchu China and the pre-Manchu China was in the same fashion in "prison", based on your assertion. The Meiji and pre-Meiji Japan was a prisoner in the same fashion. The Turks, the Romans, the Greeks and all these were in prison based you line of argument.

Political development, if there is such a thing in the real sense of the term, is a function of historical experiences and a function of time as well. The empires and nations I mentioned above had feudal and pre-feudal forms of government. Faith/religion  provided moral legitimacy in such a society.  As such monarchs were projected as ambassadors of God on earth. This applies to the Manchu monarchs, the Meiji monarchs, the caliphates (in the muslim case) and the old Christian Europe. Arms length relation between religion and state is not something peculiar to Ethiopia. Historically speaking, there were two or three occasions when  church-state relation was strained in Ethiopia to the extent that monarchs were either rejected or resisted. Merid Wolde Aregay asserted and demonstrated, convincingly, that Ethiopian emperors were not at all times dominant over Church or religion. A very good example of that is the 16th century resistance against Susnyos. My point is that church was not just a passive legitimizing entity for emperors. It was active.

The cause of Ethiopian Church, which you referred as "Ethiopian God" I think,was and continues to be, apparently the faith Christianity and Ethiopia - and whenever monarchs endanger that – their legitimacy is in jeopardy. The implication is that Church was relatively free and Church’s freedom was, apparently, meant for upholding the Church cause.

The fact that the form and purpose of freedom is in the old time is different from the purpose and form of freedom in the contemporary world does not mean that there was not freedom. Freedom was conceived as freedom from alien rule and Ethiopian church stands tall in that regard since it has profound contribution to  the survival of Ethiopian freedom – call it independence. Needless to say, the Ethiopian society was not less Christian in the past. Yet, the Ethiopian society had a clear conception of the then form of freedom. If the "Ethiopian God" was at odds with freedom, Ethiopia would not have been free in the face of formidable challenges. Freedom was collective. Society was more cohesive.

From political trajectory, in a feudal society, power relation was not democratic, so to speak. There was no such thing as individual or group right. There was no such thing as “self-determination.” Just like freedom, the conception of “self” was different in the old time. The concept and international principle of “self-determination” , as we know it in the contemporary world, is a 20th century phenomenon. The basis of power relation was consent. It was power and political marriage (even in Europe). There were times when both did not work out in Ethiopia. I would go to the extent of asserting that absolutism in Europe, as is the case elsewhere, is nothing but the gift of religion. The fact that there were times when the moral authority of monarchs (consequently their political authority) was  challenged by the Ethiopian church and “the Ethiopian God” indicates as to where centers of power were in the past. Even emperorTewodros, whom I consider as a revolutionary by any measure of the time, was a product of the “Ethiopian God.” And he never attempted challenged the "Ethiopian God." Nor embracing "Ethiopian God" prevented him from envisaging a new Ethiopia and revolutionizing the way power was assumed. So what stands between freedom and un-freedom in our time is not the “Ethiopian God.”

I would rather say,  deities hypnotizing the youth from  pursuing and attaining freedom are “modernity” , hedonism,and corrupted ,misinterpreted and sometimes over-interpreted political concepts like “self-determination." For some, "freedom" is perceived as setting "self" apart from society and rebellion against society. If we are to transcend the sociological notion of 'modernity' and embark on critical political and philosophical analysis of “modernity”, there emerges a picture that depicts “modernity” as a purely capitalist enterprise. And it manifests itself in political, economic and cultural forms.To think that "modernity" represents freedom is virtually to forget the brutes of capitalism. 'Freedom'  is promoted in a way not to challenge exploitation and profit maximizing capital.

Much more than the “Ethiopian God,” the Ethiopian Youth is corrupted by “modernity.” How many of us are aware that the European soccer teams are capitalist enterprises with the objective to maximize profit? At the same time they are also cultural tools to conquer the minds of young people. I have not done a statistical analysis but from what I observe it is not hard to imagine that millions of Ethiopians think about European soccer at least on a weekly basis, if not daily. On the other hand, how many Ethiopians think in terms of being free, as a society, from dictatorship? If any how seriously and how often?

The HolyWood world is another deity in itself. What is projected in the movies most often are lone adventurers who try to establish themselves as individual against all odds. The hero is an individual adventurer either rebelling on society or creating his own, fame fortune and world. And this came to define the meaning of life for many young minds including in Ethiopia. Service to the society and dying for country and for society came to be equated as, unofficially, something foolish. Discussing politics and discussing about the future of a country seem to have been left to "fools" or idiots.

USA is another deity. Many look up to the USA as the ideal society. Very little people seem to be  aware that the US was worse than Ethiopia in some respects. It was a country, until very recently, where institutionalized inequality is practiced. People were condemned not to attend a particular school, use a particular café or restaurant because of their colour. What Martin Luther King spoke of as a “dream” for which millions admire him was only because he thought of a time when government would do away with institutionalised segregation,people of different colour would forget their colour complexion and people won't be discriminated on the basis of their complexion. Imagine this was happening in an allegedly “liberal society” with a modern “modern constitution” and there was their own version of "God." And you think Ethiopia was imprisoned for thousands of years?

To encapsulate, the problems are “modernity” and mistaking hedonism for "freedom" and “modernity.” These are corrupting the youth and making the youth embrace a conventional and materialistic meaning of life. The fact that the projected 'freedom' is more like illusion is not noted at all.

As far as opposition groups are concerned, the notion of “self-determination” has obstructed the creation of a formidable opposition group by way of making ethnic politics appear more democratic,functional  and desirable for many. Yet, the concept of “self” which is espoused by these entities sounds rather exotic in all its forms and with no profound historical plausibility. They are embracing exclusivity. The alleged ground to embrace this exotic concept is made to appear as if it was the down sides of feudal politics more than a century ago rather than power struggle.
I suggest that deconstruction and construction project should be some where else in the area of  perception of “modernity”, "political development" and hedonism. And I like that you mentioned somewhere that modernity from within is possible. You better leave the “Ethiopian God” alone.



twitter: @dimetros

Sunday, January 23, 2011

ቡል ዶዘር!

ሲነገር ስንሰማ ...
የድሮ ወታደር
አለኝታ ነበር ለሀገር::

የዛሬ ወታደር
...አገር አፍራሽ
ከወንበር የማይገፈትር
የዘረኞች አለኝታ
ራሱ ሀገር አፋራሽ ቡል ዶዘር!


ጥር 2003, ቶሮንቶ

ሲዘምር አየነው

የሚጠፋ መስሎት እንደ ጉም የሚተን
ያገር ፍቅር በኖ ሕዝብ የሚበታተን
ቋንቋን ተገን አርጎ ሀገር ሲሸነሽን
ጭፍራ ሲያሰማራ
ወገን ሊያስፈራራ
ሰው ባገሩ እንዳይኮራ
ሀገሩን ረስቶ ዘሩን እንዲያወራ
ባንዲራ ሲቀየር
ለምን የሚለውም ሲጣል ወደ እስር
ዘዴ ቢቀያየር ...
በርሀብ በርዛት በኑሮ ቢረግጠው
ወይ ፍንክች...!
ወገን እንደሆነ ተመልሆ ያው ነው
ክልጂ እስከአዋቂ
ኢትዮጵያን ሲያስባት
ሲዘምር አየነው:: !!


ቶሮንቶ ጥር 2003

ባለፈው ሳምንት የተከበረውን የጥምቀት በዓል በኢንተርኔት ካየሁ በኍላ የተሰማኝን ስሜት ለማንጸባረቅ ነው::

Thursday, January 20, 2011

በላ ልበልሀ - ከዘመን ጋር

መቼስ ይብዛም ይነስም የሆነ ጊዜ የሕይወትን ትርጉም መጠየቃችን አይቀርም:: አንዳንዶቻችን የምንወደውን ሰው (አባት;እናት; ጓደኛ ወይንም ሌላ) ባጣን ማግስት የሕይወትን ትርጉም የምንጠይቅ አለን:: አንዳንዶቻችን ከፍቅረኛ ጋር አምባጓሮ ተፈጥሮ ስንለያይ(ብሬክ አፕ ይሉታል ፈረንጆቹ) የህይወትን ትርጉም የምንጠይቅ አለን:: አንዳንዶቻችን ደሞ ያሰብነው እቅድ ሳይሳካ ሲቀር ለዘላለሙ የማይሳካ ይመስል ወዲያው የህይወትን ትርጉም መጠየቅ የምንጀምር አለን:: ይሄ በግለሰብ ደረጃ ነው:: እንድንጠይቅ የሚያደርገን ጉዳይ እና ራዲየሱ ግን እኛ እና በእኛ ዙሪያ ባሉ ሰዎች ዙሪያ ነው:: ከዚህ ያየለ ስለ ሀገር እና ስለ ሕዝብ ሌተ ከቀን የሚታገሉ እና የሕይወትን ትርጉም በዛ የሚሰፍሩ የመንፈስ ልዕልና የገነቡ ዜጎች ደሞ አሉ:: ያው ኢትዮጵያ በታሪኳ ብዙ እንደዚህ ያሉ ግለዘቦችን አፍርታለች:: በርግጥ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በተለይ ህዋሀት አመራር ያንን የኢትዮጵያን ወርቃማ ዘመን ጨለማውን ጎኑን ብቻ በማጉላት በመንፈስ ልዕልና የኖሩ ኢትዮጵያውያንን ታሪክ ካፈራረሰው በኍላ ሌላ ታሪክ ጽፏል:: ለጊዜው እሱን ወደ ጎን እንተወው እና ለህይወት በምንሰጠው ትርጉም ውስጥ ዘመን የራሱ የሆነ ተጽዕኖ አለው የሚል ጠንኳራ እምነት አለኝ:: ለመሆኑ ከህይወት ትርጉም ጋር ተያይዞ የሚነሳ ጥያቄን ለመመለስ ዘመን የሰጠን ነገር ምንድን ነው?? ዘመን የወሰደብንስ ነገር ምንድን ነው??? በዘመን ላይ ተጽዕኖ ማሳደር ይቻላል ወይንስ ከዘመን ምርኮኛነት መውጣት አይቻልም?? በዚህ ጉዳይ ላይ እንድንወያይ እጋብዛለሁ:: በላ ልበልሀ ...

.

Friday, August 6, 2010

""ኢትዮጵያ ትቅደም!""

በሚገርም ሁኔታ ""ኢትዮጵያ ትቅደም!"" የሚለው ሀሳብ እስከዚህ ሰዐት ድረስ ; ኢትዮጵያ ትበልጽግ ወይንም ወደፊት ትራመድ ከሚል መልዕክት ውጭ ሌላ ትርጉም ያለው አይመስለኝም ነበር:: አሁን ሳስበው ግን ሀሳቡ ስነምግባራዊ (ethical) መልዕክትም የያዘ ነው::

ስግብግብነት እና ሙስና የማህበራዊ ትስስር ደንባችንን (social norm) እየገዘገዘ ሊጥለው ትንሽ ቀርቶታል በሚባልበት በዚህ ሰዐት ""ኢትዮጵያ ትቅደም"" የሚለውን ሀሳብ እንዳልባሌ እና ካለፈው የደርግ ስርአት ጋር አያይዞ በፖለቲካ መነጸር ማየቱ ትክክል አይደለም::

ያው እኛ አገር ተማርኩ የሚለውንም የህብረተሰብ ክፍል ጨምሮ ሀሳቦች ከፈረንጆች ካልተሰነዘሩ በስተቀር ወይንም የውጭ ምሁራኖች የተናገሯቸው ነገሮች ካልሆኑ በስተቀር ብዙ ቦታ ስለማይሰጣቸው እንጂ "ኢትዮጵያ ትቅደም' የሚለው ሀሳብ ጆን ኤፍ ኬኔዲ '' ሀገሬ ምን አደረገችልኝ ሳይሆን ምን አደረኩላት ብለህ ጠይቅ"" ብለው ከተናገሩት ነገር ቢበልጥ እንጂ አያንስም:: እንግዲያውስ ""ኢትዮጵያ ትቅደም"" ማለት ለኔ ለኔ አትበል ; አትስገብግብ ; መጀመሪያ ሀገርህን ኢትዮጵያን አስቀድም ማለት ነው:: አገርን ያለማስቀደም እያደረሰ ያለውን ችግር እንግዲህ ወያኔዎች በኢትዮጵያ እያደረሱት ካለው ጥፋት እና እየተከሉት ካለው የስግብግብነት እና የሙስና ባህል የበለጠ ሊያሳየን የሚችል ነገር የለም:: ኢትዮጵያን የሚመሩት ሰዎች ኢትዮጵያን ሳያስቀድሙ ከበታች ያሉት የመስተዳደሩ አካላት እንዴት ኢትዮጵያን ሊያስቀድሙ ይችላሉ???

""ኢትዮጵያ ትቅደም!"" የሚለው ሀሳብ እንደገና መንሰራራት ያለበት ሀሳብ ነው:: ኢትዮጵያ በግለሰቦች ቆዳ አትቀበርም! ዜጎቿ በኢትዮጵያ ቆዳ ይቀበራሉ እንጂ!

Sunday, July 25, 2010

"Gemena"

I love "Gemena" Drama. I love it because it vividly portrays where we are as a society. Social problems are partly reflections of governance. Put differently, social problems and/or social interaction are indicative of the nature of political system we have. Through Gemena you can see how the woyane regime is entrenching, by action or inaction, a culture of crime(crime familie), corruption, materialistic value, betrayal of freindship, greed and brutality - and all these at the expense of Ethiopian social values we used to cherish as a society. Good thing there are still sincere people who uphold the essence and values of being human. This is what we see in Gemena. It is a clarion call- a call that the social Ethiopia we used to know is collapsing - due to the action and inaction of our generation in the name of "modernity" Too bad!

Blog Archive