Monday, February 28, 2011

የዳቦ ወይስ የፖለቲካ ጥያቄ?

ድሮ ኮተቤ ኮሌጅ ስማር የረሀብ አድማ ተደርጎ ነበር:: በጊዜው የነበሩት የተማሪዎች መማክርት አባላት የህዋሀት አባልና አንዳንዶቹም ታጋይ የነበሩ ናቸው:: በደንብ አስታውሳለሁ እነዚህ አመራሮች የተሰበሰበውን ተማሪ የተጀመረው አድማ መቶ በመቶ ከምግብ አቅርቦት ጥራት ጋር የተያያዘ እንደሆነ እና የፖለቲካ ጥያቄ እንዳልሆነ አጽኖት ሰጥተው ""ፖለቲካ ከተነሳ በየለሁበትም""አይነት መንፈስ ተማሪውን ያስጠነቅቁ ነበር:: ከዚያም መፈክር ይጻፍ ተብሎ በአራት ቋንቋ ተጻፈ:: የማስታውሳቸው ""ረሀብ ጊዜ አይህብን"" ""ጋፊን ኬኛ ጋፊ እኛታቲ"" ""ጥያቄያችን የዳቦ ነው"" እና ""we demand bread"" ነበሩበት:: እውነት ለመናገር የዳቦ ችግር አልነበረም:: በእኛ ሀገር ስታንዳርድም ይቀርብልን የነበረው ምግብ አድማ የሚያስመታ አልነበረም:: እርግጥ ነው የካምፓስ ምግብ የጣዕም ችግር አለበት:: እሱ ደሞ ሀገራችን ደሀ እንደመሆኗ አድማ የሚያስመታ ጉዳይ አልነበረም:: በኍላ ሲገባኝ የምግብ ጥራት እና ""ጥያቄያችን የዳቦ ነው"" ጩኽት ትክክለኛ ምክንያት አልነበረም:: ጥያቄያቺን ""የፖለቲካ አይደለም"" የሚለውም ሀሳብ እንደዚያው::
ለአድማ ያነሳሳው ትክክለኛ ጉዳይ የታፈነ የማህበራዊ እና የፖለቲካ ችግር ነበር::

በ1992 ዓመተ ምህረትም አገሪቱን ሊያነቃንቅ የሞከረ የተማሪዎች አመጽ ተከስቶ ነበር:: የህዋሀት መንግስት ከ40 በላይ ንጹሀን ዜጎችን ገድሎበታል:: የዚህኛውም አመጽ ጥያቄ እንዲሁ ዙሪያ ጥምጥም ነበር:: ""የአካዳሚክ ነጻነት"" ጥያቄ ነበር በዋነኛነት የተስተጋባው:: ወያኔም እንደለመደው ያለ እፍረት ""ጥያቄው የአካዳሚክ ጥያቄ አይደለም:: የፖለቲካ ለውጥ ሊያመጡ የፈለጉ ኃይሎች ናቸው ያንቀሳቀሱት"" የሚል አስተሳሰብ ይዞ ተማሪውን የዘር ፖለቲካ በማራገብ ሊከፋፍለው ሞከረ:: ምናልባት ብዙዎቹ የፌስ ቡክ ጓደኞቼ የዚያ እንቅስቃሴ ቀጥተኛ ተሳታፊ የነበሩ በመሆናቸው ከላይ ያልኩትን ነገር እንደሚያስታውሱት እገምታለሁ::

ታዲያ ዛሬም ድረስ የማይገባኝ ነገር የአንድ ሀገር የዪኒቨርሲቲ ተማሪዎች ; በመሰረተ ሀሳብ ደረጃ የሀገሪቱ የወደፊት ተስፋ እና ሀገር ተረካቢ እንደመሆናቸው መጠን ቀጥተኛ የሆነ የፖለቲካ ጥያቄ መጠየቅ የማይፈቀድላቸው ለምንድን ነው?? እንደ ዜጋ የፖለቲካ መብት የላቸውም ወይ??

የኮተቤው የተማሪዎች እንቅስቃሴ ሲደረግ ወያኔ በጎጃም ገበሬዎች ላይ ይሄ ነው የማይባል ከፍተኛ በደል አድርሶባቸው ስሞታ ለማሰማት አዲስባ ድረስ የመጡበት ሁኔታ ነበር:: ተማሪው በገበሬው ላይ በተደረገው ነገር ተቃውሞን እና ሀሳቡን እንኳን እንዲገልጽ አልተፈቀደለትም ነበር:: ለምን? "" የፖለቲካ ጥያቄ"" ስለሆነ::

በተመሳሳይ ሁኔታ የ1992ም የአዲስ አበባ ዪኒቨርስቲ ተማሪዎች ""የአካዳሚክ ነጻነት"" እንቅስቃሴ ከመደረጉ ትንሽ ቀደም ብሎ ወያኔ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል በተለይም በኦሮሚያም በዜጎች ላይ ሽብር ይነዛ ነበር:: ዜጎች የኦነግ አባል ናችሁ እየተባሉ ቁም ስቅል ያዮ የነበረበት ጊዜ ነበረ:: ከኦሮሚያ አካባቢ የመጡ ተማሪዎች ተቃውሟቸውን ለማሰማት እንዴ በዮኒቨርሲቲው ጊቢ እስቅስቃሴ ሲያደርጉ የአጋዚ ሰራዊት በጨለማ ገብቶ የህዋሀት አባል ተማሪዎች መሪ ሆነው የተማሪ ወታወቂያ እየታየ ተማሪዎች ወደ እስር ተግዘዋል:: እንዲህ እንዲህ አይነት ወያኔ የሚወስዳቸው የፖለቲካ አካሄዶች ያለጥርጥር በወያኔ ፖለቲካ ላይ ጥያቄ ያስነሳሉ:: በሌላ በኩል የዮኒቨርስቲ ተማሪዎች የፖለቲካ ጥያቄ እንዲጠይቁ አይፈቀድላቸውም:: ""ጥያቄያችን የዳቦ ነው"" እየተባለ እስከመቼ ነው የሚኖረው?? የነገ ተስፋችን በማን እጂ ነው ያለው??


ሰሞኑን የግብጽ እና የቱኒዚያ ወጣቶች አብዮት አካሔዱ ብሎ የወያኔ መንግስት ሺብር ስለገባው ; ወላጆችን ሰብስቦ ልጆቻችሁን ያዙ እንዳለ ሰምተናል:: ሚገርመው ወላጆች ልጆቻቸውን የሚይዙት እኮ የፖለቲካ ጥያቄ እንዳያነሱ ነው:: በሌላ በኩል ይሄው መንግስት የኢትዮጵያ ወጣቶችን በተለያየ መልኩ እያደነዘዘ የፖለቲካ ድንፈፍ ሊያደርጋቸው እየሞከረ ነው::ቅጥ ያጣ ነቀት ማለት ይሄ ነው:: በወያኔ መንግስት ላይ ወጣቶች ሊያነሷቸው የሚገቡ ብዙ ጥያቄዎች አሉ::

እኔ ግን በዋነኛነት የምጠይቀው የህወሀት መንግስት የኢትዮጵያን ወጣቶች በስራ እድል እና በጥቅማጥቅም በመያዝ ታማኝ የስርዓቱ ተገዢዎች እንዲሆኑ የወሰደው እርምጃ ነው:: ኢትዮጵያውያን ዜጎች የትምህርት ደረጃቸው በሚፈቅድላቸው መጠን የመንግስት የስራ ዕድል የማግኘት መብት አላቸው:: ይህንን ህጋዊ መብታቸውን ዘንግተው ለስራ እድል ተብሎ የፖለቲካ እምነታቸውን መቸርቸር እና የማያምኑበትን የፖለቲካ እሳቤ እንዲያራምዱ መደረግ የለባቸውም:: የህዋሀት መንግስት በጉልበት እያስተዳደረው ባለው የኢትዮጵያ ሀብት የፖለቲካ መነገጃ የስራ ዕድል መፍጠሩ በኢትዮጵያውያን ወጣቶች እንደውለታ መታየት የለበትም :!: ህዋሀት ከኪሱ የከፈለበት ጉዳይ የለም:: እንደውም ባለፈው ከአቶ ስብሀት ነጋ በቪኦኤ እንደሰማነው ህዋሀት የትየለሌ የሆነ ሀብት እንዳጋበሰ ነው:: ያ ተረስቶ ጭራሽ ለኢትዮጵያውያን ውለታ እንዳደረገ ማሰብ ምን ያህል የፖለቲካ ድንዝዝነት እንደነገሰ ብቻ ነው የሚያሳየው::

እስከዛሬ ድረስ ቀጥተኛ የሆነ የፖለቲካ ጥያቄ ባለመጠየቅ ; የህዋሀት መንግስት የሀገሪቱን ሀብት እና ንብረት እንደፈለገው ሲያደርገው በመቆየቱ ህዋሀት የኢትዮጵያውያን ወጣቶች ውለታ አለበት:: ከገባው:: ህዋሀት ከስልጣን ከወረደ የተገኘው የስራ ዕድል ይጠፋል ብሎ ማሰብ የፖለቲካ ሞኝነትም ነው:: የኢትዮጵያ ወጣት ተስፋ ነገውን በእጁ በማስገባት እና ባለማስገባት ላይ የተመሰረተ ነው:: በህዋህት የፖለቲካ ዳረጎት አይደለም!! ህዋሀት ከስልጣን ቢሽቀነጠር ቀን የሚጭልምበት ኢትዮጵያዊ አይኖርም:: ከጨለመ የሚጭልመው ለራሱ ለህዋህት ብቻ ነው:: የፖለቲካ ለውጥ ደሞ ያስፈልጋል::ሀያ አመት ሙሉ የዘር ነጋሪት እየመታ ""በብሄር ብሄረሰቦች"" የማደናገሪያ ስልት የፖለቲካ ስልጣን በማያፈናፍን ሁኔታ ይዞ ሲዘርፍ ከኖረ የፖለቲካ ቡድን ነጻ መውጣት በራሱ ትልቅ ስኬት ነው:: ነጻነት የሌለው ወጣት ተስፋ አለኝ ሊል አይችልም! የደስታ ሆነ የስኬት; የተስፋ መሰረቱ ነጻነት ነው:: ነጻነት የሌለው ሕብረተስብ የትም ሊደርስ አይችልም::

Tuesday, February 15, 2011

ወይ ቫለንታይን?!

ሰው የመሆን ትርጉም የሚያጎላው ማሰብ እና ማገናዘብ መቻል ነው:: ከሌላው ፍጥረት የምንለይበትም ምክንያትም ይሄው ነው:: የሚያስብ እና የሚያገናዝብ ሰው ደሞ እንዳረጉት አይሆነም:: ይጠይቃል:: ""ለምን?"" ይላል:: ባለፈው በዚሁ በፌስ ብክ ፔጄ ላይ "" ዘመን የሰጠን እና የወሰደብን ነገር ምንድን ነው?"" የሚል የመወያያ ርዕስ አንስቼ የፌስ ቡክ ጓደኞች የጠበኩትን ያህል መልስ አልሰጡበትም:: እንደውም ምንም አልመለሱም:: የግብጽ ወጣቶች ሰሞኑን ትንግርት አሳይተውናል:: ዘመናዊነት የሰጣቸውን የቴክኖሎጂ ጥበብ -ኢንተርኔትን ተጠቅመው - አገሬን እወዳለሁ ይል የነበረ መሪያቸው ( ሙባረክ) የወሰደባቸውን ነጻነት በጽናት ታግለው አስመልሰውታል:: ሙባረክ የወሰደባቸውንም የትየለሌ ገንዝብ ለማስመለስ በዝግጂት ላይ ናቸው:: የተለያዩ የህብረተስብ ክፍሎች የሚገባቸውን መብት እንዲያገኙም ትግላቸውን ቀጥለዋል:: የግብጽ የለውጥ አብዮት አልቆአል ማለት አይደለም:: ከሁኔታቸው እንደተረዳሁት ትግሉን እዚህ ቦታ ላይ በቁሙ የሚጥሉትም አይመስለኝም:: እንዳልሆነ ሆኖ ሊሰበር ስለሚችል:: የግብጽ ወጣቶች የነጻነት ትግል መንፈስ ግን መንፈሳዊ ቅናት ያሳድራል:: የግብጽ ወጣቶች በዘመናቸው ላይ ተጽዕኖ ለማድረግ ሞክረዋል:: ዘመን እስከመጨረሻው ባሪያ እንዲያደርጋቸው አልፈቀዱለትም:: የግብጽ ወጣቶች ይሄንን ሁሉ ሲያደርጉ ኢትዮጵያ ውስጥ የቫለንታይንን ቀን ለማክበር በሬዲዮ እና በቴሌቭዥን ነጋሪት ይጎሰም ነበር አሉ:: አዲስ ነገር ኦንላይን ላይ ስለ ቫለንታይን ቀን የተጻፈውን አንብቤ በጣም ተገርሜአለሁ::
ወጣቱ እንደዚህ እንደዚህ አይነት -ከልብ ሆነው ሲያስቡአቸው ትርጉም የማይሰጡን አውሮፖዊ አስተሳሰቦች እና ባህሎች የሙጥኝ እያለ በያዘ ቁጥር; ትርጉም ያላቸውን እንደ ነጻነት ያሉ እና የሀገር ጉዳዮችን ቸል እያለ እና ከናካቴውም እየረሳ ይመጣል:: በመርህ ደረጃ ስናየው ፍቅር የበለጸጉ ሀገሮች ያወጡት ኮንቬንሺናል ቀን ያስፈልገዋል ወይ የሚለው ራሱ አንድ ጥያቄ ነው:: በባህልም በእምነትም እንደማውቀው ፍቅር የዕለት ተዕለት ጉዳይ ነው:: ያለፍቅር አይዋልም አይታደርም:: በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባለ ማህበረሰብ ውስጥ:: እርግጥ ነው ስጦታ ፍቅርን ይገልጽ ይሆናል:: ሀዲስ አለማየሁም ""ለሚወዱት ሰው የሚደረግ ስጦታ ከሚቀበለው ሰው ይልቅ የሚሰጠውን ሰው ልብ የበለጠ ያስደስታል"" ብለው ጽፈዋል:: ያስማማል:: ጥያቄው ግን የፍቅር መግለጫ ስጦታ ለመለዋለጥ እና ፍቅርን ለመግለጽ February 14 አይዲያል ነው ያለው ማን ነው? የቫለንታይንን ቀን myth የፈጠረው ማን ነው? ዓላማውስ ምንድን ነው ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል:: ስፔሻል የሆነ ቀን ከሆነ የሚፈለገው ""በኮንቬንሽን ደረጃ የሚከበርን ቀን የወል ይሆን እንደሁ እንጂ የግል ሊሆን አይችልም::
ከተጨባጭነት ስናየው ደሞ አውሮፖዎቹ እና አሜሪካዎቹ (ሌሎችም የበለጽጉ የእስያ ሀገሮች) የቫለንታይንን ቀን ቢያከብሩም የኢኮኖሚ ሁኔታቸው ይፈቅድላቸውል:: ጦሙን የሚያድር እና ስራ አጥ ማህበረሰብ በበዛበት ምድር ከአውሮፓዎቹ እና ከሌሎች ከሞላላቸው ሀገሮች እኩል የምናብ ቫለንታይንን የሚከበርበት ምክንያቱ ሊገባኝ አልቻለም:: ከላይ የጠቀስኳቸው ማህበረሰቦች ወጣቶች በተወሰነ መልኩ ምርታማ ናቸው:: ከዚያም ባለፈ የት ገባችሁ የት ወጣችሁ ምን አሰባችሁ የሚላቸው ጉልበተኛ መንግስት የለባቸውም:: የመንቃት እና ያለመንቃት ዕድሉ ያለው በእጃቸው ነው:: እኛ ጋር ያለው ነባራዊ ሁኔታ ሌላ:: ባለፈው ሳምንት ሀገር ቤት ስልክ ደውየ የማልጠብቀው የቅርብ ሰው ""የወያኔነት"" ፎርም ሞላሁ አለኝ:: ለምን እንደዛ ሆነ ብየ ስጠይቅ በቃ እንደዛ ካልሆነ ተምሮ ስራ ማግኘት አልተቻለም የሚል መልስ ነው ያገኘሁት:: የአንድ ሀገር ወጣት በዜግነቱ እና በችሎታው የስራ ዕድል ለማግኘት የማይችልበት ዘመን ላይ ተደርሷል ማለት ነው:: ግፈኛ የሚባለውን የደርግ አገዛዝ በደንብ አድርጌ አስታውሰዋለሁ ስዎች ስራ ለመያዝ የደርግ ፓለቲካ ደጋፊ መሆን እንዳለባቸው አላስታውስም:: አሁን ያለው መንግስት ግን በግልጽ ስራ አጥነትን ራሱ አስፋፍቶ ; የስራ ዐድልን ደሞ የፓለቲካ መነገጃ አደረገው:: የደርግ መንግስት ደሀ ነበረ:: የመንግስት ድርጂቶች እንደነበሩ አስታውሳለሁ:: ንብረትነቱ የደርግ ፖርቲ የሆነ የንግድ ተቋም እንደነበረ ግን አላስታውስም:: አንድ ጊዜ አቶ ስብሀት ነጋ የሚባሉት የህዋሀት ሰው በአሜሪካ ድምጽ የአማርኛ አገልግሎት ላይ እንደተናገሩት የህዋህት ፓርቲ እጂግ በጣም ሀብታም ነው ; መገመትም ያስቸግራል ነው ያሉት:: ይሄ ሁሉ ሀብት የተገኘው ደሞ በዛች በደሀ ሀገር ስም እና ከዛች ከደሀ ሀገርም ነው:: ስራ አጥነት ግን ተንሰራፍቷል:: ኢትዮጵያን የሚመራው የወያኔ/ህዋሀት መንግስት ደሞ ዜጎች ስራ ለማግኘት እንደ ዜጋ እንደ ኢትዮጵያዊ ሳይሆን ; የህዋሀት እና እህት ድርጂቶች ፓርቲ አባል መሆን እንደሚጠበቅባቸው እየነገረ ስራ ሲሰጥ ; ወጣቱ ህዋሀት/ኢሀዴግን እንደባለውለታ ሁሉ ያይ ጀመር አሉ:: ሚያሳዝነው ረሀቡንም ስራ አጥነቱንም የፈጠረው ( ቢያንስ ያስፋፋው) ሀዋሀት/ኢሀዴግ ሆኖ ሳለ; ይሔው ፖርቲ በፖለቲካ ወገንተኝነት መመዘኛ የስራ ሰጪ ሲሆን በጎ አድራጊ መንግስት ሁሉ ሆኖ ቁጭ አለ:: እንዳረጉት መሆን ማለት ይሄ ነው:: ይሄንን ለማሰብ ያልቻን ወይ ያልፈለግን ደርሰን ከሞላላቸው እኩል ""ቫለንታይን" ላይ ስንጠላጠል የሚገም ነገር ነው::

ዛሬ የቫለንታይንን ቀን ምክንያት አድርጌ አነሳሁት እንጂ የፈረንጆች አዲስ ዓመት ሲከበር አዲስ አበባ ሻራተን ጠጠር መጣያ እስከሚጠፋ ሰው ሞልቶ አበሻው የፈረንጆችን በዓል ቁጥር እይቆጠረ አክብሯል:: ""የኢትዮጵያ ቴሌቭዢንም"" ስርጭቱን በቀጥታ አስተላልፏል:: የምናስብ ትውልዶች ነን ለማለት ማስረጃ ማግኘት ሁሉ እየከበደኝ ነው:: ያ ሁሉ ነገር ሻራተን አዲስ ቢቀርም ኖሮ እኮ አንድ ነገር ነበር:: ሌላኛው ያልገባው ወጣት እንዲጓጓለት ተደርጎ በቀጥታ በቴሌቭዥን መተላለፉ ነው የሚያስቆጨው:: በየገጠሩ እና በክፍለ ሀገር ከተሞች ያለው ወጣት ያንን እያየ ኢትዮጵያ "አድጋለች"" እያለ እንዲሳሳት እና ማንነቱ እንዲወናበድበት እየተደረገ ነው ያለው:: ከታች ያለውን ክሊፕ ተመልከቱ::

http://www.youtube.com/watch?v=VceDMjlfLdQ

የኢትዮጵያውይንም ገና እየተረሳ "' x-mass'" ላይ ትኩረት እየተሰጠ እንደመጣ ነው የሚሰማው:: ትውልዳችንን እንዳረጉት እየሆነ ነው:: የሚያደርጉት ደሞ ራሱን ሳይሆን ሌላ አይነት::እየሆነ ያለውን ነገር ሁሉ ዝም ብለን በዘመን ተጽዕኖ ሂሳብ መያዝ አለብን? ነው ጠንከር ያለ ነገር አለ?? ማነው እየመራን ያለው? ወዴት ነው እየተመራን ያለነው? አሁን የተያዘው አካሄድስ ያስፈልገናል ወይ? የኢትዮጵያ ባህል አደንዛዥ ነው ጎታች ነው ...ምናምን ምናምን እየተባለ ሌላ አንደንዛዥ የሰው ሀገር ባህል እና አስተሳሰብ ያስፈልገናል ወይ? በእርግጥ የህይወት ትርጉሙ ምንድን ነው? ማንስ ነው የሚተረጉምልን? የደስታ ምንጩ ምንድን ነው?

በዚህ ጉዳይ ላይ ሀሳብ ብንለዋወጥ በጣም ደስ ይለኛል ::

Thursday, February 3, 2011

"I blow out first ..."

This evening I happened to listen to a conversation between two teenage boys in men's locker room in a gym. I will refer to them as B1 and B2.

B1: listen I've a question. My girl friend blow out a lot. Do you argue with your girlfriend very often?
B2: We do.
B1: like on big...big issues?
B2: We even argue on every little issues
B1: Who blows out first?
B2: depends. If I didn't eat I blow out first. lol

Saturday, January 29, 2011

እስከመቼ?!

ተሸክሞ የብሶት ቁልል
ችጋርና ርሀብ ቤቱን ሰርቶ
ቁራሽ ምኞት ሆኖ አርፎ
በፈረቃ እየተበላ ስንቱ
በየቤቱ ራሱን ስቶ
ቁራሽ ፍለጋ ተከልቶ
ቀየውን መንደሩን ትቶ;
ከሁለት ያጣ እንዲሉ
ቁራሹም ጠፍቶ ላመሉ
ቀየውንም ቁራሹንም እየተራበ
ጉደኛ አሳዳሪ...
""ዕድገት"" አለ እያለ ከበሮ ደረበ::

"" ህዳሔ አለ ...ዕድገት አለ
አስፋልት ተነጠፈ
ጥርጊያ መንገድ ተደለደለ
ለዕድገት ተብሎ..
ለአረቡ; ለቻይናው; ለህንዱ መሬት ታደለ
ዕድገት አለ:: ""

እንዲህ አይነት ፌዝ እየሰማ
አበሽ ልቡ እየደማ
በረሀብ የሚፈጀው
ረሀብ እና ባርነት ያደረጀ 'ሚታገሰው
እስከመቼ ነው?!

የ""አትንኩኝ"" ባይነት መንፈስ
ነጻነት ባበቀለበት ምድር
ዛሬ "አትንኩኙን" ማን ቀጠፈው
ማን ቀላቀለበት ከአፈር::

ምነው አበሽ ዝምታ አበዛ አንገቱን ሰበረ
"'ከመናገር ደጃዝማቺነት ይቀራል"" ተረስቶ
ስለምን ለዘራፊ አሳዳሪ አቀረቀረ??

ኧረ እንደልማድህ አበሽ
ኑር እንደ አባት አደሩ
ችጋር; ባርነት ለሚደግስ
እስከመቼ እሺሩሩ??



ጥር 2003 ቶሮንቶ

Monday, January 24, 2011

Leave the Ethiopian God alone

This was a response to a discussio on facebook

In light of the experience of France and other European countries, a major change, (I am avoiding to use the terminology revolution as there is a lot of stigma attached to it,) is preceded by a period of intellectual discourse. The discourse is meant to understand the kind of change needed and explore impediments to effect those changes. I salute you for taking the initiative to trigger discussion on this matter. Indeed it is high time to question as to what stands between the need for freedom and the apparent success of dictatorship to avert change in Ethiopia.


For me,the problem has a lot to do with consciousness (in its social and political form). Yet, you were bold enough to throw the cross on the “Ethiopian God” and the Ethiopian church as major factors affecting change – change towards Freedom. If I capture you correctly, your premise runs something like “Ethiopia has been in prison for thousands of years” and you advanced the argument that “ Ethiopia’s true imprisoner [captor] is her own creation, her own God.” And you concluded by suggesting creation of a new God.

To begin with I don’t agree with the assertion that "Ethiopia has been in prison for thousands of years." What exactly is prison? It sounds that by prison you are making reference to Ethiopian Christianity. Christianity is not a faith that Ethiopia created. Rather Ethiopia took Christianity very seriously. Do you know of any society that is not influenced by this or that form of faith/religion?  Are you asserting Ethiopia's imprisonment on the basis of modern political thinking? If that is the case, which empire and/or nation in the world could be free from this allegation? Which country was not in "prison" for millennium? The politics of the past –especially that of thousands of yearscould/should not be analyzed on the basis of “modern” political thinking. Pre-modern Europe was conservative, monarchical and Christian too. The Manchu China and the pre-Manchu China was in the same fashion in "prison", based on your assertion. The Meiji and pre-Meiji Japan was a prisoner in the same fashion. The Turks, the Romans, the Greeks and all these were in prison based you line of argument.

Political development, if there is such a thing in the real sense of the term, is a function of historical experiences and a function of time as well. The empires and nations I mentioned above had feudal and pre-feudal forms of government. Faith/religion  provided moral legitimacy in such a society.  As such monarchs were projected as ambassadors of God on earth. This applies to the Manchu monarchs, the Meiji monarchs, the caliphates (in the muslim case) and the old Christian Europe. Arms length relation between religion and state is not something peculiar to Ethiopia. Historically speaking, there were two or three occasions when  church-state relation was strained in Ethiopia to the extent that monarchs were either rejected or resisted. Merid Wolde Aregay asserted and demonstrated, convincingly, that Ethiopian emperors were not at all times dominant over Church or religion. A very good example of that is the 16th century resistance against Susnyos. My point is that church was not just a passive legitimizing entity for emperors. It was active.

The cause of Ethiopian Church, which you referred as "Ethiopian God" I think,was and continues to be, apparently the faith Christianity and Ethiopia - and whenever monarchs endanger that – their legitimacy is in jeopardy. The implication is that Church was relatively free and Church’s freedom was, apparently, meant for upholding the Church cause.

The fact that the form and purpose of freedom is in the old time is different from the purpose and form of freedom in the contemporary world does not mean that there was not freedom. Freedom was conceived as freedom from alien rule and Ethiopian church stands tall in that regard since it has profound contribution to  the survival of Ethiopian freedom – call it independence. Needless to say, the Ethiopian society was not less Christian in the past. Yet, the Ethiopian society had a clear conception of the then form of freedom. If the "Ethiopian God" was at odds with freedom, Ethiopia would not have been free in the face of formidable challenges. Freedom was collective. Society was more cohesive.

From political trajectory, in a feudal society, power relation was not democratic, so to speak. There was no such thing as individual or group right. There was no such thing as “self-determination.” Just like freedom, the conception of “self” was different in the old time. The concept and international principle of “self-determination” , as we know it in the contemporary world, is a 20th century phenomenon. The basis of power relation was consent. It was power and political marriage (even in Europe). There were times when both did not work out in Ethiopia. I would go to the extent of asserting that absolutism in Europe, as is the case elsewhere, is nothing but the gift of religion. The fact that there were times when the moral authority of monarchs (consequently their political authority) was  challenged by the Ethiopian church and “the Ethiopian God” indicates as to where centers of power were in the past. Even emperorTewodros, whom I consider as a revolutionary by any measure of the time, was a product of the “Ethiopian God.” And he never attempted challenged the "Ethiopian God." Nor embracing "Ethiopian God" prevented him from envisaging a new Ethiopia and revolutionizing the way power was assumed. So what stands between freedom and un-freedom in our time is not the “Ethiopian God.”

I would rather say,  deities hypnotizing the youth from  pursuing and attaining freedom are “modernity” , hedonism,and corrupted ,misinterpreted and sometimes over-interpreted political concepts like “self-determination." For some, "freedom" is perceived as setting "self" apart from society and rebellion against society. If we are to transcend the sociological notion of 'modernity' and embark on critical political and philosophical analysis of “modernity”, there emerges a picture that depicts “modernity” as a purely capitalist enterprise. And it manifests itself in political, economic and cultural forms.To think that "modernity" represents freedom is virtually to forget the brutes of capitalism. 'Freedom'  is promoted in a way not to challenge exploitation and profit maximizing capital.

Much more than the “Ethiopian God,” the Ethiopian Youth is corrupted by “modernity.” How many of us are aware that the European soccer teams are capitalist enterprises with the objective to maximize profit? At the same time they are also cultural tools to conquer the minds of young people. I have not done a statistical analysis but from what I observe it is not hard to imagine that millions of Ethiopians think about European soccer at least on a weekly basis, if not daily. On the other hand, how many Ethiopians think in terms of being free, as a society, from dictatorship? If any how seriously and how often?

The HolyWood world is another deity in itself. What is projected in the movies most often are lone adventurers who try to establish themselves as individual against all odds. The hero is an individual adventurer either rebelling on society or creating his own, fame fortune and world. And this came to define the meaning of life for many young minds including in Ethiopia. Service to the society and dying for country and for society came to be equated as, unofficially, something foolish. Discussing politics and discussing about the future of a country seem to have been left to "fools" or idiots.

USA is another deity. Many look up to the USA as the ideal society. Very little people seem to be  aware that the US was worse than Ethiopia in some respects. It was a country, until very recently, where institutionalized inequality is practiced. People were condemned not to attend a particular school, use a particular café or restaurant because of their colour. What Martin Luther King spoke of as a “dream” for which millions admire him was only because he thought of a time when government would do away with institutionalised segregation,people of different colour would forget their colour complexion and people won't be discriminated on the basis of their complexion. Imagine this was happening in an allegedly “liberal society” with a modern “modern constitution” and there was their own version of "God." And you think Ethiopia was imprisoned for thousands of years?

To encapsulate, the problems are “modernity” and mistaking hedonism for "freedom" and “modernity.” These are corrupting the youth and making the youth embrace a conventional and materialistic meaning of life. The fact that the projected 'freedom' is more like illusion is not noted at all.

As far as opposition groups are concerned, the notion of “self-determination” has obstructed the creation of a formidable opposition group by way of making ethnic politics appear more democratic,functional  and desirable for many. Yet, the concept of “self” which is espoused by these entities sounds rather exotic in all its forms and with no profound historical plausibility. They are embracing exclusivity. The alleged ground to embrace this exotic concept is made to appear as if it was the down sides of feudal politics more than a century ago rather than power struggle.
I suggest that deconstruction and construction project should be some where else in the area of  perception of “modernity”, "political development" and hedonism. And I like that you mentioned somewhere that modernity from within is possible. You better leave the “Ethiopian God” alone.



twitter: @dimetros

Sunday, January 23, 2011

ቡል ዶዘር!

ሲነገር ስንሰማ ...
የድሮ ወታደር
አለኝታ ነበር ለሀገር::

የዛሬ ወታደር
...አገር አፍራሽ
ከወንበር የማይገፈትር
የዘረኞች አለኝታ
ራሱ ሀገር አፋራሽ ቡል ዶዘር!


ጥር 2003, ቶሮንቶ

ሲዘምር አየነው

የሚጠፋ መስሎት እንደ ጉም የሚተን
ያገር ፍቅር በኖ ሕዝብ የሚበታተን
ቋንቋን ተገን አርጎ ሀገር ሲሸነሽን
ጭፍራ ሲያሰማራ
ወገን ሊያስፈራራ
ሰው ባገሩ እንዳይኮራ
ሀገሩን ረስቶ ዘሩን እንዲያወራ
ባንዲራ ሲቀየር
ለምን የሚለውም ሲጣል ወደ እስር
ዘዴ ቢቀያየር ...
በርሀብ በርዛት በኑሮ ቢረግጠው
ወይ ፍንክች...!
ወገን እንደሆነ ተመልሆ ያው ነው
ክልጂ እስከአዋቂ
ኢትዮጵያን ሲያስባት
ሲዘምር አየነው:: !!


ቶሮንቶ ጥር 2003

ባለፈው ሳምንት የተከበረውን የጥምቀት በዓል በኢንተርኔት ካየሁ በኍላ የተሰማኝን ስሜት ለማንጸባረቅ ነው::

Thursday, January 20, 2011

በላ ልበልሀ - ከዘመን ጋር

መቼስ ይብዛም ይነስም የሆነ ጊዜ የሕይወትን ትርጉም መጠየቃችን አይቀርም:: አንዳንዶቻችን የምንወደውን ሰው (አባት;እናት; ጓደኛ ወይንም ሌላ) ባጣን ማግስት የሕይወትን ትርጉም የምንጠይቅ አለን:: አንዳንዶቻችን ከፍቅረኛ ጋር አምባጓሮ ተፈጥሮ ስንለያይ(ብሬክ አፕ ይሉታል ፈረንጆቹ) የህይወትን ትርጉም የምንጠይቅ አለን:: አንዳንዶቻችን ደሞ ያሰብነው እቅድ ሳይሳካ ሲቀር ለዘላለሙ የማይሳካ ይመስል ወዲያው የህይወትን ትርጉም መጠየቅ የምንጀምር አለን:: ይሄ በግለሰብ ደረጃ ነው:: እንድንጠይቅ የሚያደርገን ጉዳይ እና ራዲየሱ ግን እኛ እና በእኛ ዙሪያ ባሉ ሰዎች ዙሪያ ነው:: ከዚህ ያየለ ስለ ሀገር እና ስለ ሕዝብ ሌተ ከቀን የሚታገሉ እና የሕይወትን ትርጉም በዛ የሚሰፍሩ የመንፈስ ልዕልና የገነቡ ዜጎች ደሞ አሉ:: ያው ኢትዮጵያ በታሪኳ ብዙ እንደዚህ ያሉ ግለዘቦችን አፍርታለች:: በርግጥ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በተለይ ህዋሀት አመራር ያንን የኢትዮጵያን ወርቃማ ዘመን ጨለማውን ጎኑን ብቻ በማጉላት በመንፈስ ልዕልና የኖሩ ኢትዮጵያውያንን ታሪክ ካፈራረሰው በኍላ ሌላ ታሪክ ጽፏል:: ለጊዜው እሱን ወደ ጎን እንተወው እና ለህይወት በምንሰጠው ትርጉም ውስጥ ዘመን የራሱ የሆነ ተጽዕኖ አለው የሚል ጠንኳራ እምነት አለኝ:: ለመሆኑ ከህይወት ትርጉም ጋር ተያይዞ የሚነሳ ጥያቄን ለመመለስ ዘመን የሰጠን ነገር ምንድን ነው?? ዘመን የወሰደብንስ ነገር ምንድን ነው??? በዘመን ላይ ተጽዕኖ ማሳደር ይቻላል ወይንስ ከዘመን ምርኮኛነት መውጣት አይቻልም?? በዚህ ጉዳይ ላይ እንድንወያይ እጋብዛለሁ:: በላ ልበልሀ ...

.

Friday, August 6, 2010

""ኢትዮጵያ ትቅደም!""

በሚገርም ሁኔታ ""ኢትዮጵያ ትቅደም!"" የሚለው ሀሳብ እስከዚህ ሰዐት ድረስ ; ኢትዮጵያ ትበልጽግ ወይንም ወደፊት ትራመድ ከሚል መልዕክት ውጭ ሌላ ትርጉም ያለው አይመስለኝም ነበር:: አሁን ሳስበው ግን ሀሳቡ ስነምግባራዊ (ethical) መልዕክትም የያዘ ነው::

ስግብግብነት እና ሙስና የማህበራዊ ትስስር ደንባችንን (social norm) እየገዘገዘ ሊጥለው ትንሽ ቀርቶታል በሚባልበት በዚህ ሰዐት ""ኢትዮጵያ ትቅደም"" የሚለውን ሀሳብ እንዳልባሌ እና ካለፈው የደርግ ስርአት ጋር አያይዞ በፖለቲካ መነጸር ማየቱ ትክክል አይደለም::

ያው እኛ አገር ተማርኩ የሚለውንም የህብረተሰብ ክፍል ጨምሮ ሀሳቦች ከፈረንጆች ካልተሰነዘሩ በስተቀር ወይንም የውጭ ምሁራኖች የተናገሯቸው ነገሮች ካልሆኑ በስተቀር ብዙ ቦታ ስለማይሰጣቸው እንጂ "ኢትዮጵያ ትቅደም' የሚለው ሀሳብ ጆን ኤፍ ኬኔዲ '' ሀገሬ ምን አደረገችልኝ ሳይሆን ምን አደረኩላት ብለህ ጠይቅ"" ብለው ከተናገሩት ነገር ቢበልጥ እንጂ አያንስም:: እንግዲያውስ ""ኢትዮጵያ ትቅደም"" ማለት ለኔ ለኔ አትበል ; አትስገብግብ ; መጀመሪያ ሀገርህን ኢትዮጵያን አስቀድም ማለት ነው:: አገርን ያለማስቀደም እያደረሰ ያለውን ችግር እንግዲህ ወያኔዎች በኢትዮጵያ እያደረሱት ካለው ጥፋት እና እየተከሉት ካለው የስግብግብነት እና የሙስና ባህል የበለጠ ሊያሳየን የሚችል ነገር የለም:: ኢትዮጵያን የሚመሩት ሰዎች ኢትዮጵያን ሳያስቀድሙ ከበታች ያሉት የመስተዳደሩ አካላት እንዴት ኢትዮጵያን ሊያስቀድሙ ይችላሉ???

""ኢትዮጵያ ትቅደም!"" የሚለው ሀሳብ እንደገና መንሰራራት ያለበት ሀሳብ ነው:: ኢትዮጵያ በግለሰቦች ቆዳ አትቀበርም! ዜጎቿ በኢትዮጵያ ቆዳ ይቀበራሉ እንጂ!

Sunday, July 25, 2010

"Gemena"

I love "Gemena" Drama. I love it because it vividly portrays where we are as a society. Social problems are partly reflections of governance. Put differently, social problems and/or social interaction are indicative of the nature of political system we have. Through Gemena you can see how the woyane regime is entrenching, by action or inaction, a culture of crime(crime familie), corruption, materialistic value, betrayal of freindship, greed and brutality - and all these at the expense of Ethiopian social values we used to cherish as a society. Good thing there are still sincere people who uphold the essence and values of being human. This is what we see in Gemena. It is a clarion call- a call that the social Ethiopia we used to know is collapsing - due to the action and inaction of our generation in the name of "modernity" Too bad!

Monday, March 1, 2010

አደዋ !

ነገረ አድዋ ...ጥልቅ ; ምጥቅ
ጸአዳ ዝንት -ዓለም የሚያንጸባርቅ

የወራሪ የታሪክ ለምጥ
የአበሽ የታሪክ ጌጥ
የአበሽ ተድላ ሀሴት
የወራሪ የመንፈስ ; የአካል ስብራት

አድዋ የቀን አውራ
የድል አባወራ
እንዳውዳመት ይዘከራ !

የድል ብስራት
የድል ጥሪት
የመንፈስ ስንቅ ያበሻ አንጡራ ሀብት

አድዋ !
የወንድነት ድካ ያበሽነት ልክ ስፍር
የአበሽ የድል ገድል ! የድል ስንክሳር
የድል ችቦ ክምር
የማይበገር ጀግና ትውልድ
የደም ; ያጥንት ውልድ
ሲያስቡት መንፈስ እንደ ችቦ የሚያቀጣጥል የሚያነድ
የኛነታችን ማህተም የኛነታችን አሻራ
የመንፈስ መጽናኛ በሌሎች ጥቁር ሕዝቦችም ጎራ

አድዋ !

የአበሻነት እና ""የነጻነት "' የቃል ኪዳን ውል
የእምቢ ለሀገሬ እምቢ ለነጻነቴ ብሂል
የሚንበለበል ያገር ፍቅር ምስል
"ዋ ኢትዮጵያ ! እኔ ላንቺ ልሙት እረ ልከንበል "
ይሄ ነው ያድዋ ትርጉሙ
ሃበሻ የጻፈው የሳለው በደሙ

ሰው ሲደመም ጡብ ;ሲሚንቶ ;ፌሮ ተስማምቶ ሰማይ ሊነካ ሲንጠራራ
አበሽ በዛቱ ; በልቡ የማይፈርስ ሰማይ ጠቀስ የድል ክምር ሲሰራ
የሚታይ ከየትኛውም ስፍራ ...
እኛማ ለምን አንኮራ !!

አድዋ ትዕይንትም ነው
በአንድ በኩል ቀልበ ጡሊ የሰው አገር ሊወር የወበራ
በሌላ በኩል ገራገር አበሽ ግን ለነጻነቱ የማይመለስ ሞት የማይፈራ
ስንት የሴት ወንድ ; ስንት የወንድ አውራ
ጎራዴ የያዙ እጆች የተፋለሙበት ከባለመትረየስ ጋራ
የስጋና የመንፈስ ስምምነት የ "ልሙት ለሀገሬ ፍካሬ '
የጽኑ ነብስ ; ጽኑ ስጋ የመንፈስ ዝማሬ ; የተጋድሎ ፍሬ
ያገር ፍቅር እና አልሸነፍ ባይነት
ወራሪን እንደ ሰንጋ የመተሩበት
ያበሻ ማንነት የታየበት
ዝንታለም የሚታወስ ትዕይንት

አደዋ !

የአድዋስ ቅዱስነት !!!
እንደ ክርስቶስ ስቅለት
ለሰው ልጂ ፍቅሩን እንደገለጠበት
አበሻ "ለነጻነት ' ያለውን ቀናዒነት ያሳየበት
የደም ; ያጥንት አስራት በኩራት ያስገባበት
የነጻነት የመጨረሻ ዋጋ -ህቅታውን ከነዛቱ የሰጠበት
የድል ጥሪት ;
የአበሽ መንፈሳዊ ሀብት !!
የሀበሻ ኩራት !!

አድዋ የድል አውራ
እንደ አውደ ዐመት ይከበራ !!

Wednesday, December 30, 2009

Women, Relationship and marriage

A friend of mine wrote this on his facebook page: "Because they[women] are the custodians of the egg, and take nine months to bear a baby. And they are the primary caretakers of the very young in every culture in the world. So women are exceedingly valuable, because they are the ones who will rear a man's DNA."

I decided to kick off discussion on this topic partly because his view reflects my conception of women -My version of admiring nature transcends flora and fauna, a sunset on the beach, mountains and things like that. I admire beauty ( i call it nature) in the same fashion, if not more. Partly because I noticed the unease that exists vis-a-vis relationship( and marriage) in North American Society.

My friend's view of women reflects the importance of women by virtue of their nature...which is true. This is even a divine construction...and it is important not only in terms of ensuring continuity of humanity but also for the sucess of one's life on individual basis.Unfortunately, it is pervassive in this part of the world that women are seen as a problem. Women, on their part, complain a lot about men.

During my first year in Toronto, I was so surprised to see ads for a "cheaper and quick divorce service" in every single bus stops.Then I asked, myself, "what is wrong with advanced society?" Very soon I realized that relationship is over politicized and legalized.There is a lot of expectation, "do's" and "don'ts" on both sides and you can tell that things would go wrong from the very beginning. I would say that the catalyst is Liberalism. Liberalism is like a faith and it is injected to all aspects of societal life. Relationship and marriage is not an exception.On top of that Hedonism and pop culture has its own negative impact on relationship. In consequence, you have incredible number of single mothers, single fathers and single men and women in their 30's. Also in consequence,Relation is feared. It is clear that the problem is contributing to the crime rate.

I would say relationship is entirely an emotional and spiritual enterprise. And as such it should not be politicized by way of emphasizing rights and caged in a legal realm. Ethiopia has something to offer in this regard. I am of the view that marriage , as a concept and practice, in Ethiopia represents a spiritual and emotional construction. This is not to say that there is no problematic marriage in Ethiopia.No! But predominantly marriage is a success stroy. There is no emphasis on rights.Mutual recognition of the importance of one another is what matters most. "Ante tibes anchi tibishi" is the norm -not an emphasis on rights which is a political construction.And I don't think that "quick divorce" service of lawyers, as things stands now, will have a market in a society like Ethiopia. So my whole point is that true women are really important...but relationship and marriage in a society like where live, North America, is so much strained by the notion of liberalism, femminism and obviously the offshoot is doubt towards relationship, a society dominated by singles and even crime. Marrriage should be kept out of the reach of politics and the philosopy of liberalism. Relationship and marriage need to emphasize emotion rather that rights -which is both a political and legal construction. I really like the terminologies "soulmate" and "significant other."
They seem to indicate more the spiritual and emotional nature of relationship.Your thoughts on this please

YouTube - Bezawit Zeleke

YouTube - Bezawit Zeleke

Saturday, December 12, 2009

የሰው ዕብቅ

ስልጣኔ አዙሮት እራሱን የሳተ
በሰው ንፍዘት እየዋተተ
በነውር በሀጢያት እየተደሰተ
ራሱን ለሰዶምነት እየፈተተ
ሰልጥኛለሁ ይለናላ
ወደ ሰዶም እየሄደ ወደ ኌላ
ኧረ እግዚያብሔር ኢትዮጵያን ጠብቅ
እንዳያረክሳት እንዲህ ያለ የሰው ዕብቅ

Friday, December 4, 2009

ውጪ ሀገር

ነገሩን ለማያቅ ውጪ የሚባለው ስሙ ቢያስደስትም
ውስጡ ለቄስ ይሁን እንደስሙ አይደለም
ብዙ ቢባልለት አኗሪ አንቀባሮ
የተወለወለ ቢያስመስል ብርሌ ገጽን አሳምሮ
ባይታይ ነው እንጂ ብዙው ከውስጥ ጠቁሮ
በደስታ ደህይቶ ይኖራል እሮሮ
አይ የውጭ አገር ኑሮ !!!

ሰው ባባይ ይፈርዳል

ሰው ባባይ ይፈርዳል
ዓባይም ይጮሀል
ግና መች ይሰማል
ወንዝ አለቱ ቢሆንም መንገደኛነቱ
ማን ጩኸቱን ሰማ
ማንስ ቦታ ሰጠው እንዲያድር በቤቱ
ኧረ ጎበዝ ካባይ ራስ ውረዱ
ቦታ ባልሰጠነው
በቀየው ባላሳደርነው ;በኛው ፍረዱ !

Friday, October 9, 2009

አለ አንዳንድ ሰዐት

አለ እኮ አንዳንድ ሰዐት
ለራስ የሀሴት መለከት የሚነፉበት
ከራስ ጋር በሰላም በፍቅር የሚጫወቱበት
አሁንን የሚያጣጥሙበት
ነገር ዓለሙን ረስቶ
አሮጌ ፋይል ዘግቶ
ቀልብን ለሀሴት አመቻችቶ
በቃ ነገር ዓለሙን ትቶ
......ጉራንጉሩን ረስቶ
ልብ እና መንፈስን አስማምቶ
ትላንት እና ነገን ወርውሮ
አሁንን በአሁን አጥሮ
እንዲሁ... በአሁን መደመም
ትላንት ሳይታሰብ...ነገ ሳይታለም
እንዲህ ያለ ሰዐት አያስደስትም!

ጥቅምት 2, 2002 ዓ.ም

ሀሚልተን

Friday, October 2, 2009

ተስፋ የሚያስፈልገው ተስፋ አስቆራጭ በሚመስል ሁኔታ ነው

በትምህርት ቤቴ ቤተ መጽሐፍት ሰማይን ማየት በሚያስችለኝ
ቦታ ምቾት ባለው ወንበር ላይ ተቀምጫለሁ
የያዝኩትን ዳጎስ ያለ መጽሀፍ አነባለሁ
በተመስጦ ጉዳዪን እያኘኩ ገጾቹን ላፍ ላፍ አደርጋለሁ
አንዳንዴ ደሞ ንባቡን ትቼ እቆዝማለሁ
አይኔን ወደ ውጭ ልኬ ከምድር እስከ ሰማይ ማየት የቻልኩትን ነገር ሁሉ እማትራለሁ ::

አንዲት ነጭ ርግብ እየበረረች ተፋትልካ
ከመስታወቱ ተጋጭታ ለማጥመጃ የተቀመጠ የሚመስል የቆመ ሺቦ ላይ ብትሰካ
ልቤ በሀዘን ተነካ ::
ሁለቱም ክንፎቿ በሽቦው ተቸነከረ
የውስጧም ውሀ ፈሰሰ ወደታች ተንቆረቆረ
አንዱ እንደኔ ያያት መስታዎቱን ነካክቶ ለማስበረር ሞከረ ::

ልክ ሞቷን ለመጠባበቅ እንደመረጠች ነገር
እርግቧ አልቻለችም ትንሽ እንኳ ለመብረር መሞከር
ጸጥ አለች .
ግን ትተነፍሳለች ::
ልጁ ተስፋ ቆርጦ ተመለሰ
የኔም እጀ ወደ መጸሀፌ ተመለሰ ...ጠረጴዛውን ዳሰሰ
ንባቡን ብጀምርም እይታየ ትንሽ ደፈረሰ
ብዙ ደቂቃ ቢያልፍም አይኔ ከአንድ አንቀጽ አልፎ የትም አልደረሰ ::

ያኔ ንባቡን መልሼ አቆምኩ
እርግቧን እያየሁ መቆዘሜን ቀጥልኩ ::

እንዳንቀላፋች ናት
""ግን የታል የፈጠራት ?
እውነት ሁሉንም የፈጠረው እግዚያብሔር ነው ?"" እያልኩ
ከእግዜር ሙግት ጀመርኩ
ጥርጣሬየን አጠናከርኩ ::

"'ሰውስ እሺ ሀጢያት ይሰራል ይባል
አሁን ይቺ ርግብ ምን ይወጣታል
በእውነት ፈጥሯት ከሆነስ እንዴት ዝም ይላል
እንዴት ሞት ይፈረድባታል ??""
እያልኩ እንደሞተች ተስፋ በመቁረጥ
ግን ደሞ መሞቷንም በውል ለማረጋገጥ
መስታወቱን በጣቴ ብቆረቁር
እርግቧ ወደ ላይ ተነስታ መብረር
ወዲያው ደንግጨ ወይ እግዚያብሔር !!!
አፌ ተሳሰረ
ልቤም በጸጸት እና በእምነት ተሰበረ ::
በእኔ ብሶ በእግዚያብሄር ስላዘንኩ
እጂጉን ተጸጸትኩ
ማንበቡንም ትቼ ወደ ቤት ተመለስኩ
ያሳለፍኩትን የጥርጣሬ ዘመን በአእምሮየ ከለስኩ
አንድ ነገር አወኩ !
ለካስ ተስፋ የሚያስፈልገው
ተስፋ አስቆራጭ በሚመስል ሁኔታ ነው :
ተስፋም እግዚያብሔር ነው ::

በፈረንጆቹ በዲሴምበር ወር 2007 ላይ ትምህርት ቤት ያጋጠመኝ ነው ::

ቶሮንቶ
ተጻፈ ዛሬ ሐምሌ 12, 2001 ዓ .ም

Blog Archive